Friday, January 30, 2015

US urges Ethiopia to ensure fair trial to bloggers and journalists

January 30, 2015
(U.S. Department of State) The United States is concerned by the Ethiopian Federal High Court’s January 28, 2015, decision to proceed with the trial of six bloggers and three independent journalists on charges under the Anti-Terrorism Proclamation. The decision undermines a free and open media environment—critical elements for credible and democratic elections, which Ethiopia will hold in May 2015.US on Ethiopian bloggers
We urge the Ethiopian government to ensure that the trial is fair, transparent, and in compliance with Ethiopia’s constitutional guarantees and international human rights obligations. We also urge the Ethiopian government to ensure that the trial is free of political influence and continues to be open to public observation.
The use of the Anti-Terrorism Proclamation in previous cases against journalists, activists, and opposition political figures raises serious questions about the implementation of the law and about the sanctity of Ethiopians’ constitutionally guaranteed rights to freedom of the press and freedom of expression.
Freedom of expression and freedom of the press are fundamental elements of a democratic society. We call on the government of Ethiopia to support freedom of expression and freedom of the press to demonstrate its commitment to democracy as it approaches its May 2015 national elections.

Thursday, January 22, 2015

የሕሊና እስረኛዋ ርዕዮት ዓለሙ ልደት: ከርዕዮት በጎውን እንቅና !

ዙርያን በመመልከት ካለንበት መጀመር ለምንም ነገር የተሻለ ነው፤ ከቤተሰብህ፣ከጓደኛ፣ከማህበረሰብ ራስን ለመረዳት እና ትርጉም ያለው ሥራ ለመስራት፣ በጎውን ለማድረግ ብንቀና ለስኬታችን ቀላል መንገድ ነው፡፡ ለዚህም ይመስላል “በጎውንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቀችሁ ማን ነው ? በማላት በጴጥ.መ.ምዕ 3ቁ 13 ላይ ተገልፆ ይገኛል ፡፡
1310 ቀን በእስር እያሣለፈች የምትገኘው፣የተወዳጇ የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ የልደት በዓል ፣እጅግ በጣም ደስ በሚል ሁኔታ በድምቀት ተከብሯአል፡፡ በልደት ቀኗ ተዋቂ ግለሰቦች፣የፓለቲካ ፓርቲ መሪዎች እና አባላት፣ጋዜጠኞች፣የማህበራዊ-ድረ ገፅ ዋንኛ አንቀሳቃሾች፣ ጓደኞቿ እና ቤተሰብ በመገኘት የበዓሉ ተካፋይ ለመሆን ችለዋል፡፡ በቦታው በመገኘት ፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም፣ፕ/ር በየነ ጴጥሮስ፣ኢ/ር ይልቃል ጌትነት እንዲሁም አቶ በላይ በፍቃዱ በተሰጣቸው አጭር ደቂቃ በመጠቀም ለርዮት መልካ ልደት ከመመኘት በላፈ ፣አስደማሚ ንንግር አድረገዋል፡፡
reyot alemu
በተለይ ፕ/ር መስፍን ያደረጉት ንግግር እና ያስተላለፉት መልዕክት በሁሉም ዘንድ አድናቆት የተቸረው ልብን ሰርስሮ የሚገባ ነው፡፡ አቶ በላይ በበኩላቻው ያደረጉት ንግግር የተጀመረው ሠላማዊ ትግል ለደቂቃ ያካል ወደኋላ ሣይል፣ ተጠናክሮ መቀጠል እናዳለበት እና ለዚህም በመትጋት ርዕዮት እና መሰሎቻ የእስር ጊዜ ለማሣጠር ያስተላላፉት መልዕክት እና ለተግባራዊነቱ የሚባክን ጊዜ አለመኖር ያመላከቱበት ንግግር በታዳሚው ዘንድ ተደማጭነት ያገኘ ሃሳብ ነው፡፡ኢ/ር ይልቃል ከርዕዮት ጋር ካለቸው ቀረቤታ መነሻ በማድረግ ፣መሠረታዊ የሆነ የርዕዮት የሁል ጊዜ ፀባይ ደፈርነት እና ግልፅነት በማስታወስ፣የሰው ልጅ እነዚህን ፀባይ ከአድር-ባይነት ተላቆ በአስታዋይነት የሁሉ ጊዜ ተግባሩ ካደረግ ፣ለየትኛውም ስኬት ቅርብ ነው፡፡ለዚህም ደግሞ ምስክር የምትሆነን ርዕዮት ናት በማላት ሁሉን አመላካች የሆነው ምርጥ ንግግር አድርገዋል፡፡
ከምንም በላይ ደግሞ በቃሊት እስር ቤት 1310 ቀን በስቃይ እያሳለፈች የምትገኘው ጋዜጠኛ እና መምእርት ርዮት አለሙ፡፡ አሁንም ደከመኝ ሰለቸኝ ሣትል የሁል ጊዜ እምነቷ በሆነው ሰላማዊ ትግል ያላት ተስፋ ሣይደበዝዝ፤ ለፓርቲ መሪዎች እና ለፖለቲካ ፓርቲ አባላት ያስተላላፈችው መልዕክት ነው፡፡የመልዕክቷ ዋንኛ ማጠጠኛ እውነተኛ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ቢቻል አንድ ሆነው ፣ካልሆነም ተከባብረው በሰላማዊ ትግል በአጭር ጊዜ አምባገነኑን ሥርዓት በማሸነፍ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ የስልጣን ባለቤትነት እንዲያረጋግጡ ተማፅኖ ያልተለየው መልዕክቷ ፣ ከአምባገነን አገዛዝ ወደ-ዲሞክራሳዊ ለውጥ ለሚደረገው ትግል የሞራል ስንቅ መሆኑ ፣መልዕክቱ ተነቦ እንዳለቀ የነበረው ጭብጨባ እና አድናቆት አማላካች ነበር፡፡
ሻምፓኝ ተከፍቶ ወዲኽ-ወዲያ መወዛወዝ ባይኖርም ፣በግጥም ሥራው ብዙ አድናቂ ያተረፈው ፤በተለይ በማህበራዊ ድረ-ገፅ በሚያስገርሙ ግጥሞቹ የሚያስደስተን፣ ገጣሚ ዮሐንስ ሞላ ለርዕዮት መልካም ልደት ተመኝቶ ያቀረበው ግጥም ታዳሚውን ያስደመመ ነበር፡፡ የፋክት መፅሔት ም/ክ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ኃይለመስቀል በሸዋመምየለህ እና ጋዜጠኛ ስለሺ አጎስ እንደ-ቅደም ተከተላቸው ያቀረብት ፁሑፍ፣ የዕለቱን ፕሮግራም ፈካ በማድረግ ፁሑፍ ፃሃፊ ብቻ ሣይሆን ምርጥ አንባቢ መሆናቸውን አስመስክረወል፡፡
Journalist Reeyot Alemu
Journalist Reeyot Alemu
እነዚህ ከላይ የገለፅኳቸው በዛሬው ዕለት ቀበና በሚገኘው አንደነት ፓርቲ ፅ/ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ከተከናወኑ ድረጊቶች በከፊል ነው፡፡በአጠቃላይ በዛሬው እለቱ የተገኙት በሙሉ እኔን ጨምሮ ለርዕዮት ልደት ነው፡፡ ርዕዮትን የሚያስታውስ አስከንድር ነጋ ፣ ተመሰገን ደሣለኝ፣ የሱፍ ሐመድን፣ውብሸት ታዬ፣ ዞን ዘጠኝ ጦማሪያን በፍፁም አይረሳም፡፡ስለ ርዕዮት እስር የሚጨነቅ ናትናኤል መኮንን፣አንዱአለም አረጌ፣አበበ ቀስቶ፣አብታሙ አያሌው፣ዳንኤል ሽበሺ፣የሺዋስ አሰፋ፣አብርሃ ደስታ፣አግባው ሰጠኝ እና ሌሎች የፖለቲካ እስረኛ ለመርሳት እንዴትም አይቻለውም፡፡ ስለ ርዕዮት ፍትህ ማጣት የሚያንገበግበው ሁሉ የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ለሰኮንድም አይዘነጋቸውም ፡፡ሁሉም አንድ የሚያደርጋቸው ለነፃነት እና ለፍትህ የከፈሉት ዋጋ ነው ! ይህ ነገራቸው ደግሞ ያስቀናል፡፡ እናም በጎውንም ለማድረግ ብንቀና የሚያስጨንቀን ማን ነው ?”
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላላም ትኑር !

Wednesday, January 21, 2015

Journalist Reeyot: Prisoner of conscience continues in defiance to TPLF/EPDRF prison

The recent article posted on several websites entitled ” metaram yemgebaw manew” (መታረም የሚገባው ማነው) by Journalist Reeyot Alemu caught my eyehttp://www.abugidainfo.com/amharic/index.php/16788.Reeyot Alemu is a budding Ethiopian poet, essayist, and journalist.
Reeyot is a winner of the 2013 UNESCO-Guillermo Cano World Press Freedom Prize. She is one of the many political conscience prisoners in Ethiopia. Based the regime so called anti-Terrorist Law which is designed to suppress free speech and fundamental democracy rights of the Ethiopian people, she has been thrown to jail. She was regarded as a “terrorist” and jailed in the infamous prison of Kaliti, initially sentenced to twelve years later reduced to five years. Her detention is the result of judicial proceedings that are clearly unfair. Since her detention the Ethiopians civic organizations and other humanitarian organization called for her and other prisoner of conscience to immediate and unconditionally release. To this date the ruling party TPLF/EPDRF regime refused to release her.
We have read dozens of articles about political prisoners who had experienced the terror, torture, and the solitary confinement in Mekelawi and Kailti prisons. Both prisons have a notorious reputation when it comes to dealing with political detainees. The prisoners are subject to ruthless TPLF interrogator with harsh and life threatening condition. She was not allowed to speak to her lawyer to contest the charge against her, and to see or speak to her family members or friends for extended time. She stated that all her rights were abused . It is clear that she doesn’t want to reveal to the readers all brutality used by the police interrogators, but she indicated a hint. She – said the interrogator slapped her on her face and bangs her head to prison wall to shake her down. You may guess what is happeningnext.
Based on her article it appears that she is at the end of her prison term. The authorities demanded her to sign a paper entitled “ተመክሮ”. Judging from title it might contains a broadarray of restrictions on her rights and movements, , or statutory declaration accepting the accusation. Knowing the ruling party behavior, it is one of the oppressive tactics to dehumanizing and degrading political prisoners. Nevertheless, whatever the intent of the paper is, she decided not sign “ተመክሮ”.
Reeyot’s message has been the same, fight back. She is determined to defend the honorable causes of justice, equal rights, free speech and press for all Ethiopians. She is paying the sacrifice for what she believes. With her fight, she has demonstrated resisting pressure from jailers to accept any conditions that affect her to live as free person is important enough to pay even more price. As saying goes “the truth shall set you free”. She is not looking for special favor or a gesture of good will. She flatly refused to accept a release by trading-off between her principle and “so called ተመክሮ”. The jailers made her health condition worse by not allowing her to have hospital treatment. Our political process has become so messed up that no legendary figure available to look for inspiration. Reeyot is one of crusader of free press freedom and an advocate of social justice for all Ethiopians.
TPLF/EPDRF’s crimes on Reeyout and Ethiopian people are ruthless. The regime is similar to Stalin, Pol Pot and other dictators in the world. They have been demonstrating merciless behavior to its own people the past 22 years. Fair minded people have to fight systematically for replacement of this tyrant. As the fight continues, one would hope things often changes for better. After all who would have imagined that the Arab spring would oust their dictators? This will happen in Ethiopia too. Reeyot’s principle and her story set an example to peaceful movement in recent Ethiopia history. She is one of an ordinary citizen that refused to admit crime which she never committed. All admired her guts and courage of conviction in battling her breast cancer as well as the complete idiotic jailers’ ill treatments. She decided to fight rather than quietly live in servitude.
No one naively believes that TPLF/EPDRF’s will change its behaviors. We have no option other than fighting back like Reeyot. As saying goes “No matter how epically monstrous TPLF/EPDRF becomes, the struggle does not end with them to get freedom. It only begins with them”.

Saturday, January 17, 2015

ወያኔ ኢትዮጵያን አፍርሶ ወደ ጉሬው ለመግባት የመጨረሻ መሠናዶውን እያደረገ ነው

  • የትግሬ-ወያኔዎች ከተለያዩ ጎሣዎች እና ነገዶች ሰዎችን መልምለው እና አደራጅተው፣ እንዲሁም የወታደራዊ፣ የደህንነት፣ የአደረጃጀት፣ የአመራር እና የቁጥጥር ሥራ የሚሠሩ የትግሬ-ወያኔዎች መድበው በከፍተኛ ሚሥጢር ኢትዮጵያን የማፈራረስ ሤራ እየተዶለቱ መሆኑን በተጨባጭ መረጃዎች አረጋግጠናል።
የትግሬ-ወያኔ የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያን በመበታተን፣ የትግራይ ረፑብሊክ መመሥረት መሆኑን በ1968 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው ፕሮግራሙ መሠረት ላለፉት ፵(አርባ) ዓመታት ያደረገው ጉዞ ያሣያል። በጉዞው የኢትዮጵያን የረጅም ዘመን ታሪክ ክዶ በመቶ ዓመት መገደቡን፣ የትግሬ-ወያኔ መሪዎች እና አባሎች በተደጋጋሚ በጻፉዋቸው መጻሕፍት እና በየአጋጣሚው ባደረጉዋቸው ንግግሮች ለሕዝብ ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል። «ኤርትራ በኢትዮጵያ በቅኝ ግዛትነት የተያዘች ናት፤ ስለሆነም ሻዕቢያ የሚያካሂደው የመገንጠል እና የነፃነት ጥያቄ ተገቢ እና ትክክል ነው።» ብለው፣ ከሻዕቢያ በላይ ሻቢያ ሆነው፣ የትግራይን ልጆች የጦር ማገዶ በማድረግ ኤርትራን ማስገንጠላቸው ማንም ሊያስተባብለው የማይችለው ሃቅ ነው። ኢትዮጵያውያንን እንደ አንድ ሕዝብ ያስተሳሰሩ የወል ዕሴቶችን፥ «የኢትዮጵያዊነት አገራዊ እና ብሔራዊ ስሜት የሁሉም በኢትዮጵያ የሚኖሩ ነገዶች እና ጎሣዎች ሳይሆኑ፣ የዐማራው ብቻ የማንነት መገለጫዎች ናቸው፤ ዐማራው ጨቋኝ እና በዝባዥ ነገድ ነው፤ እርሱን ሁሉም ነገዶች እና ጎሣዎች በወያኔ መሪነት ተባብረው ማጥፋት አለባቸው።» በማለት በከፈቱት የዘር ማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ጦርነት፣ የኢትዮጵያዊነት የወል ዕሴቶችን፣ ተቋሞችን፣ ግንኙነቶችን፣ አሠራሮችን ወዘተርፈ በማጥፋታቸው ዛሬ አገሪቱ እና ሕዝቧ የሚገኙበት ሁኔታ በግልጽ ያሣያል። የአገሪቱ ዘመን-ጠገብ መልከዐ-ምድራዊ መለያ ስሞች እና ወሰኖች ተሽረው በተወሰኑ ነገዶች ማንነት ብቻ ላይ የተመሠረቱ ስሞች በመስጠት፣ የኢትዮጵያውያንን ተዘዋውሮ በፈለጉት ቦታ እና አካባቢ የመኖር እና የመሥራት ተፈጥሮአዊ፣ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና ሰብአዊ መብቶቻቸውን ገፍፈው፣ አንድነታቸውን አሣጥተው፣ አብሮነታቸውን ክደው፣ በጠላትነት እንዲተያዩ አድርገዋቸዋል። ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ከሕዝቡ ስሜት ፈጽሞ እንዲጠፉ መጠነ ሠፊ የሆነ የሥነልቦና ጦርነት ከፍተው አገሪቱን ከመጨረሻው የጥፋት ጠርዝ ላይ አድርሰዋት ይገኛሉ።
የትግሬ-ወያኔ እና ተከታዮቹ በኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት፣ ሉዓላዊነት እና ብሔራዊ ጥቅም፣ እንዲሁም በሕዝቧ ኢትዮጵያዊ ማንነት ላይ ታሪክ፣ ትውልድ፣ ሕግ እና ማናቸውም ዓይነት ሥነ-ምግባር ይቅር ሊለው የማይችል የክህደት ተግባሮችን የፈጸሙ መሆኑን ከማንም ይበልጥ ራሣቸውም አይክዱም። ይህም በመሆኑ የኢትዮጵያ አንድነት ተጠብቆ ከዘለቀ በየትኛውም ጊዜ በአገር ክህደት ወንጀል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ያውቃሉ። ከዚህ ተጠያቂነት ለመዳን እንችላለን ብለው የሚምኑት ሁለት ነገሮችን ጎን ለጎን ማከናወን ሲችሉ ብቻ  ነው። እነዚህም፦ አንደኛ የወያኔ ትውልድ ለሚቀጥሉት መቶ ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሕይዎት ላይ የወሳኝነቱን ሚና ይዞ የሚቀጥልበት አስተማማኝ ሁኔታ  ሲረጋገጥ፤ ይህ የመጀመሪያው ዕቅድ በተለያዩ ምክንያቶች ባይሣካ ሁለተኛው አማራጭ ዕቅድ ትግራይን ከኢትዮጵያ በመገንጠል የትግራይ ረፑብሊክ በመመሥረት ጎጆ መውጣት፤ የሚሉ ናቸው።
Eth
ሁለተኛውን ግብ ለማሣካት በኢትዮጵያ ላይ ሥልጣን ከተቆጣጠሩ ጊዜ ጀምሮ ለምትገነጠለው ትግራይ ቁሣዊ፣ ቴክኒካዊ እና ኅሊናዊ ሁኔታዎች እንዲሟሉ የሚያስችሉ ተግባሮችን ማከናወን እንዳለባቸው ታሣቢ አድርገው መንቀሣቀሣቸው ባለፉት ፳፫(ሃያ ሦሥት) ዓመታት የሥልጣን ዘመናቸው  ትግራይ ውስጥ አያሌ የመሠረተ ልማት ሥራዎች መሥራታቸው ይታወቃል። በዚህም መሠረት የትግራይ ክልል ከጎንደር እና ከወሎ ክፍለ ሀገሮች መሬት ነጥቀው በታሪክ የትግራይ አካል ሆነው የማያውቁ አካባቢዎችን አጠቃልለው ጥንተ-ነዋሪውን የዐማራ ነገድ አባላት የሚገድሉትን በመግደል፣ ቀሪውን በማሠር እና በማሰደድ ትግሬን አስፍረውበታል። ይህ የያዙት ግዛት ወደፊት ለምትገነጠለው ትግራይ ይጠብባል በማለት ከሰቲት ወደ ደቡብ ምዕራባዊ የጎንደር እና የጎጃምን የሱዳን አዋሳኝ ወረዳዎችን ከቤንሻጉል ጉምዝ እና ጋምቤላ ክልሎች ጋር በማገናኘት የታላቋ ትግራይን የመሥፋፋት ዓላማ ዕውን በማድረግ ላይ ይገኛሉ (አባሪ ካርታውን ይመልከቱ)።
በዚህም መሠረት ለወደፊቷ ትግራይ ለምትጠቀልለው ሠፊ ግዛት፣ ከውጭው ዓለም ጋር የሚያገናኙ የመገናኛ መሥመሮችን ዘርግተዋል፣ ተጨማሪ መሥመሮችንም በፍጥነትም በመገንባት ላይ ይገኛሉ። የትግራይን ምርት ወደ ውጭ ለመላክ እና ከውጭ የሚፈለጉ ሸቀጦችን ወደ ውስጥ ለማስገባት፣ ከጅቡቲ እስከ መቀሌ፣ ከሱዳን ጠረፍ እስከ መቀሌ የሚያገኛኙ የባቡር ሐዲድ ግንባታዎች በመፋጠን ላይ ናቸው። ሁለት ታላላቅ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ጣቢያዎች መቀሌ እና አክሱም ላይ ገንብተዋል። ቀበሌዎችን ከወረዳ ከተሞች፣ ወረዳዎችን ከአውራጃዎች (ዞኖች)፣ አውራጃዎችን ከዋና ከተማዋ ከመቀሌ ጋር የሚያገናኙ፣ ክረምት ከበጋ ያለምንም እንከን አገልግሎት የሚሠጡ መረብ-መሰል አውራ መንገዶች ተገንብተዋል። ድርቅን  ለመቋቋም የክረምት ዝናብን ለማቆር የሚያስችሉ በርካታ ግድቦችን ሠርተው አገልግሎት ላይ አውለዋል። የትግራይን አዲሱን ትውልድ ከኢትዮጵያዊነት ስሜት አውጥቶ የትግራዊነት ስሜት እንዲገነባ የሚያስችሉ፣ በተቀነባበረ ሁኔታ ቅስቀሣ እና ትምህርት በማያቋርጥ መልኩ የሚሰጡ ተቋሞች ተገንብተዋል። በርካታ ትምህርት ቤቶች፣ ኮሌጆች፣ የቴክኒክ እና የሙያ ትምህርት ቤቶች፣ ዩኒቨርስቲዎች ተከፍተዋል። በኢንዱስትሪ ግንባታ ረገድ የነባሮቹን የኢትዮጵያ ፋብሪካዎች ሕልውና የሚያጠፉ የመድኃኒት፣ የጨርቃጨርቅ፣ የስሚንቶ፣ የመጠጥ እና የብረታ ብረት ፋብሪካዎች በሁሉም የትግራይ አውራጃዎች ተቋቁመዋል። ከእነዚህ መካከል፦ የአዲግራት መድኃኒት ፋብሪካ፣ እንዲሁም መቀሌ የተገነቡት የመሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ፣ የአልሜዳ የጨርቃጨር ፋብሪካ፤ የመሥፍን ኢንጂነሪንግ የብረታ ብረት ኢንዱስትሪ፣ ወዘተርፈ ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው። አሽጎዳ አካባቢ በአፍሪቃ በግዙፍነቱ ቀዳሚ የሆነ እና በነፋስ ኃይል ኤሌክትሪክ የሚያመነጩ ተርባይኖች በብዛት ተገንብተዋል።
የአገሪቱ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መዋቅሮች ያላአንዳች ይሉኝታ በወያኔች የተያዙ ናቸው። የአገሪቱን የአየር እና የምድር ኃይል መከላከያ የማዘዣ ማዕከሎች ከአዲስ አበባ እና ከደብረዘይት በማስወጣት ማዕከላዊ ዕዛቸውን ትግራይ ላይ እንዲሆን በማድረግ ወሣኝ የሆኑት የመከላከያ መሣሪያዎች ትግራይ ውስጥ እንዲከማቹ ተደርጓል። የከባድ ሮኬቶች መተኮሻ መንኮራኩሮች ትግራይ ውስጥ ተገንብተዋል። የአገሪቱ የመከላከያ ኃይል ከጓድ እስከ ጠቅላይ ኤታማጆር ሹም ድረስ ያሉት ቁልፍ የአዛዥነት፣ የመገናኛ፣ የድርጅት፣ የሎጂስቲክ ኃላፊነቶችን በሙሉ በትግሬዎች በማስያዝ የወታደራዊ ተቋሙ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴው የትግራይን መገንጠል ዕውን በሚያደርግ መልኩ ወደፊት እየተባለ ይገኛል።
በአጠቃላይ የትግራይን ግንጠላ ዕውን መሆን ሂደቱ የተመቻቸ እንዲሆን፣ በ«ሽግግር ዘመን» ተብየው «ልማት ቅድሚያ በጦርነት ለተጎዱ ክልሎች» በሚል ስም የአገሪቱ  አጠቃላይ በጀት ለትግራይ ልማት ተመድቦ ለአምስት ዓመታት ከላይ ለተጠቀሱት ተግባሮች እንዲውል መደረጉ ይታወቃል። ከሽግግር መንግሥቱ ፍጻሜ በኋላም የተዘጋጀው «ሕገመንግሥት» ተብየው የሽግግር መንግሥቱ ቻርተር ተከታይ ሆኖ በመዘጋጀቱ፣ አጠቃላይ ያለፉት ፳፫(ሃያ ሦሥት) ዓመታት ሲሠራ የኖረው ከፍ ሲል የተጠቀሱትን ሁለት ግቦች ለማሟላት፣ ማለትም፦ የትግሬ-ወያኔ ትውልድ ለመቶ ዓመታት በኢትዮጵያ ሥልጣን ላይ የሚቆይበትን ሁኔታ እያረጋገጡ መጓዝ፣ ይህ የማይሆን ከሆነ ለምትገነጠለው ትግራይ ቁሣዊ፣ ቴክኒካዊ እና ኅሊናዊ መሠረት ሊሆኑ የሚችሉ የሁለንተናዊ ግንባታ ተግባሮችን በተጓዳኝ ማከናወን የሚለው በተደጋጋፊ መልኩ ሲሠራ መቆየቱ ይታወቃል።
ይህ ሁሉ ሤራ ቢጎነጎንም፣ የትግሬ-ወያኔ ባልጠበቀው መልኩ የኢትዮጵያዊነት ስሜት ከሕዝቡ ኅሊና ውስጥ ከመፋቅ እና ከመደብዘዝ በተቃራኒ፣ የበለጠ እየጠነከረ መሄዱ የአደባባይ ምሥጢር ነው። ለዚህ ማረጋገጫዎች በተከታታይ በሚነሱ ሕዝባዊ ተቃውሞዎች እና በተቃዋሚ ኃይሎች መበራከት ናቸው። ስለዚህ የትግሬ-ወያኔ ቡድን «ለመቶ ዓመታት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሥልጣን ላይ እቆያለሁ» የሚለው ዓላማው ሊሣካ የማይችል እንደሆነ፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ በ፲፱፻፺፯ (1997) ዓ.ም. ብሔራዊ ምርጫ በማረጋገጡ፣ አጠቃላይ እንቅስቃሴውን «ትግራይን ከቀሪዋ ኢትዮጵያ መገንጠል» በሚለው ሁለተኛ ግቡ ላይ እንዲያተኩር ሁኔታዎች እንዳስገደዱት ይታያል። ለዚህ የግንጠላ ዓላማው ያጸደቀው «ሕገመንግሥት» ተብየው ዋናው መሣሪያው መሆኑ ይታወቃል። አንቀፅ ፴፱(ሰላሣ ዘጠኝ) ለማንም ጥቅም ተብሎ ሣይሆን፣ የትግራይን ግንጠላ ለማሣሳካት የተቀረጸ አንቀፅ እንደሆነ ማንም ይስተዋል አይባልም። ዛሬም ቢሆን የትግሬ-ወያኔ የተመሠረተበትን ዋናውን ስሙን (ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ) ያለመቀየሩ የሚያረጋግጠው ሃቅ ትግራይን ከቀሪዋ ኢትዮጵያ መገነጠል በይደር የቆየ የማይቀር አጀንዳው መሆኑን ነው። ይህ ዕውነት እንደተጠበቀ ሆኖ በዚህ አንቀፅ ብቻ ትግራይን ገንጥሎ በሰላም መኖር እንደማይችል የትግሬ-ወያኔ ጠንቅቆ ያውቃል። የትግሬ-ወያኔ መሪዎች ከተጠያቂነት መዳን የሚችሉት፣ ከኢትዮጵያ ሕዝብ የዘረፉትን ንብረት መጠቀም የሚችሉት፣ የትግራይ መገንጠል ለጊዜውም ቢሆን ዕውን ሊሆን የሚመችለው፣ በቀሪዋ ኢትዮጵያ ነገዶች መካከል መበታተን ሲፈጠር፣ ከሁሉም በላይ ዐማራ የተሰኘውን ነገድ ሌሎች ነገዶች በጠላትነት ፈርጀው እርሱን ማዳከም ሲችሉ፣ እንዲሁም «ዐማራ» ሲል የከለለውን ክልል ከውጭ አገር ጋር እንዳይገናኝ ዝግ በማድረግ ብቻውን አቁሞ ኅልውናውን ማጥፋት ሲቻል እንደሆነ ብቻ መሆኑን ይህ ቡድን አቅዶ በተግባር ሲንቀሣቀስ ቆይቷል። ለዚህም ባለፉት ዓመታት ሁሉም በሚባልበት ደረጃ በአገሪቱ ውስጥ የሚገኙት ነገዶች ዐማራውን በአውራ ጠላትነት ፈርጀው የጥፋት እጃቸውን እንዲያነሱበት አድርጓል።
የትግሬ-ወያኔ ምዕራባዊውን «የዐማራውን ክልል» ለም እና ድንግል መሬቶች ለሱዳን በገጸበረከት ሰጥቷል። በቀረው ምዕራባዊ ዳርቻ የትግራይን ግዛት በማስፋት ከቦ፣ ከቤንሻጉል ጉምዝ እናከጋምቤላ ክልሎች ጋር አገናኝቷል (አባሪ ካርታውን ይመልከቱ)። ከ5 ሚሊዮን የማያንስ ዐማራ ከምድረ ኢትዮጵያ አጥፍቷል። አያሌ ዐማሮች በአገር ውስጥ ሠርቶ የመኖር መብታቸውን በመገፈፋቸው ለስደት ሕይዎት ተዳርገዋል። በስደት በዓለም ዙሪያ ከሚኖረው ኢትዮጵያዊ መካከል ከመቶ ፷(ስድሣ) እጁ በላይ ዐማራ መሆኑ የሚያመለክተው፣ ዐማራው በገዛ አገሩ ሠርቶ የመኖር መብቱን የተገፈፈ መሆኑን ብቻ ሣይሆን፣ ዐማራው በመጥፋት ሂደት ላይ መሆኑን የሚያሣይ ነው።
ሰሞኑን ለሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት ከደረሱት እጅግ አስተማማኝ መረጃዎች መካከል፣ ወያኔ በኢትዮጵያ ፖለቲካ አናት ላይ የመቆየት ዓላማው የማይሣካ መሆኑን ተገንዝቦ፣ ወደ ሁለተኛው እና የመጨረሻ ግቡ፣ ማለትም፦ ትግራይን ለመገንጠል በከፍተኛ ሚስጢር እየሠራ መሆኑን የሚያረጋግጡ ናቸው። ይህም የትግራይ ግንጠላ ዕቅድ ለማሣካት እንዲቻል፣ ከአገር ውስጥ ተቃዋሚ ኃይል እንዳይነሣ፣ ኢትዮጵያን በሽግግር ዘመኑ ከፋፍለዋት በነበረው ፲፬(አሥራ አራት) እና ከዚያም በላይ የሆኑ የክልል ወሰኖችን የሚያመለክቱ ካርታዎችን አዘጋጅተው፣ ከየጎሣው ሰዎችን መልምለውና አደራጅተው፣ ለነዚህ ሰዎች የወታደራዊ፣ የደህንነት፣ የአደረጃጀት፣ የአመራር እና የቁጥጥር ሥራ የሚሠሩ የትግሬ-ወያኔዎች ተመድበው በከፍተኛ ሚሥጢር ፀረ-ኢትዮጵያ ሤራ እየተዶለተ መሆኑን አረጋግጠናል። ይህም ከ1997 የምርጫ ሽንፈታቸው ማግሥት ጀምሮ በመከናወን ላይ ያለ ተግባር እንደሆነ የመረጃ ምንጮቻን ገልፀውልናል። «ይህ አይሆንም፣ አይደረግም፣ አይታሰብም» ሊባል የማይችል እንደሆነ የወያኔ ጉዞ እና ተግባር ከጥርጣሬ ውጭ በሆነ መንገድ ያስረዳናል። ለዚህ ሤራቸው ማረጋገጫዎቹ በነባር ኢትዮጵያዊ እምነቶች መካከል እየሰራ ያለው የማጥፋት ሥራ፤ በጎጃም፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባ፣ በሶማሌ፣ እየተካሄዱ ያሉት የጥፋት እርምጃዎች የዚህ ዕቅድ አካሎች መሆናቸውን ልብ ሊባል ይገባዋል።
ሌላው የትግሬ-ወያኔ ኢትዮጵያን የማፈራረስ ተልዕኮው የማይቀር እና የፍጻሜው የመጨረሻ ደረጃ ላይ መድረሱን ማሣያው፣ የምዕራቡ ዓለም የመረጃ እና የስትራቴጂክ ጥናቶች ተቋም ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት አጋማሽ ላይ በ2030 እ.አ.አ. ከዓለም ካርታ ላይ ከሚጠፉ አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗን ይፋ ማድረጉን እናስታውሳለን። በተመሣሣይ ሁኔታ በኅዳር ወር ፪ሺህ፯ ዓ.ም. ሞስኮ ውስጥ የተካሄደ የዓለም አቀፍ ቀውሶች ጥናት ተቋም ባዘጋጀው ስብሰባ፣ በምሥራቅ አፍሪካ የሚታየውን ብጥብጥ ለዘለቄታው ለማስወገድ የምሥራቅ አፍሪካ አገሮች ኮንፌደሬሽን መመሥረት እንዳለበት ግፊት የሚያደርግ ጥናት ቀርቧል። የኮንፈደሬስሽኑ አባል አገሮች ጥንት እንግሊዝ «ከኢትትዮጵያ ተቆርሶ ወደ ሱዳን ይካተት» ትለው የነበረው የኤርትራ ምዕራባዊ ክፍል ወደ ሱዳን ተካልሎ ሱዳን ከሦስት እንድትከፈል፣ የኤርትራ ደጋማው ክፍል ከትግራይ ጋር ተቀላቅሎ ትግራይ ትግርኝ የተሰኘ ግዛት እንዲፈጠር፣ የአፋርኛ ተናጋሪዎች በአንድ ግዛት ተጠቃለው አንድ ግዛት እንዲሆኑ፣ በአምስቱ ዓመት የአርበኛነት ዘመን ፋሽስት ጣሊያን «ዐማራ» ብሎ ሰይሞት የነበረው ክልል አንድ የዐማራ ግዛት እንዲሆን፣ የቀሩት አካባቢዎች የፋሽስት ጣሊያንን ክፍፍል መሠረት አድርገው የየራሳቸውን ግዛቶች እንዲመሠረቱ እና በነዚህ አገሮች መካከል ኮንፌደሬሽን ይመሥረት የሚል ነው። የእነዚህ ጥናቶች ግብም ከወዲሁ ኢትዮጵያዊው የኢትዮጵያን መፍረስ አይቀሬነት እንዲለማመደውና «ድሮም ተብሎ ነበር» በማለት የአገሩን መፍረስ በፀጋ እንዲቀበል የሥነ- ልቦና ሰለባ ከወዲሁ መሠራቱን የሚያመለክቱ ናቸው።
ካርታ፦ ለወደፊቱ «የትግራይ ሪፑብሊክ» ተብሎ በትግሬ-ወያኔ የሚገነጠለው የኢትዮጵያ አካል በአረንጓዴ ቀለም የተቀለመው ነው።
የትግሬ-ወያኔ እና ዕኩይ ዓላማው ኅልው ሆነው የሚዘልቁት ኢትዮጵያውያን ሠፊውን ለቀን ጠባቡን፣ ኢትዮጵያዊነትን ትተን ጎሣዊ ማንነትን ስንላበስ፣ ዕውነትን ከድተን ከውሸት ጎራ ስንሰለፍ፣ ዘላቂውን ትተን አላቂውን እና ጠፊውን ስንይዝ፣ አኩሪውን ትተን  ነገ የሚያሳፍረውን ስንከተል፣ ለኅሊና ሳይሆን ለጥቅም ስንገዛ ነው። እስካሁን የትግሬ-ወያኔ ያለ ልጓም የጋለበን በነዚህ ምክንያቶች ብቻ ነው። አሁን ግን የትግሬ-ወያኔ አጥፍቶን ሊጠፋ ከመጨረሻው ጠርዝ ላይ ቆሟል። የመጥፋቱም ያለመጥፋቱም ጉዳይ የሚወሰነው በእኛ ብቸኛ ምርጫ ነው። ምርጫችን በኢትዮጵያዊነታችን መቀጠል ከሆነ፣ ወያኔ ያጠመደልንን የመነጣጠል መንገድ ትተን በአንድነት በመቆም ኢትዮጵያን ከመጥፋት ለመታደግ ቁርጠኛ አቋም ልንይዝ ይገባል። ቢመሽም፣ እጅግ ብንዘገይም፣ ፈጽሞ ከመቅረት ይሻላል እና እጅ ለጅ ተያይዘን አገራችን እንድናድን ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ጥሪውን ያቀርባል።
ከሁሉም በላይ የትግሬ-ወያኔ ወደ መጨረሻ እርምጃው ሲያመራ አጥፍቶ የሚጓዘው፣ ከጽንሱ ጀምሮ በአውራ ጠላትነት ፈርጆ ላለፉት ፵(አርባ) ዓመታት ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሲገድለው፣ ሲያስረው፣ ሲያሰቃየው እና ሲያሳድደው የኖረውን ዐማራ እስትንፋስ ሳያቋርቋጥ ከጉሬው እንደማይገባ አውቀን፣ ከተደገሰልን ጥፋት እራሳችን መከላከል እንድንችል ከምንጊዜውም በላይ ነቅተንና ተደራጅተን ኅልውናችን ለማስጠበቅ ቁርጠኛ ሆነን እንድንቆም ሞረሽ-ወገኔ አደራ ይላል።

Wednesday, January 14, 2015

Zambia: Grappling with Ethiopian illegal immigrants

CHIMWEMWE MWALE, Lusaka – HARDLY a month passes without news about a dozen or more foreign nationals being arrested mostly for illegal entry or stay in Zambia or both.News of their illegal entry into the country in containerised trucks, among other unorthodox means of entry into the country, is perhaps not strange anymore.Zambia Ethiopian illegal immigrants
The Immigration Department is on record of having thwarted several other isolated incidences and attempts by some foreign nationals to illegally enter and perhaps stay in Zambia.
Despite the department’s watchful eye, Zambia continues to record an influx ofillegal immigrants, who sometimes use un-gazetted paths owing to the porous nature of the country’s vast border lines.
The latest and last episode to ‘swathe’ 2014 was when the Immigration Department (Chinsali regional office) arrested 16 male Ethiopians aged between 16 and 22 years on December 29.
The foreign nationals were found locked in a house in the border town of Nakonde. The house belonged to a suspected human trafficker identified as Justin Sikazwe.
According to a statement released by Immigration Department public relations officerNamati Nshinka, immigration officers were successfully led to the house by a named Zambian.
Mr Nshinka said Mr Sikazwe was not found at the time of the raid.
“However, the 16 Ethiopians were discovered after the officers compelled Mr Sikazwe’s wife to open the door to the house. The Zambian who led the officers to the house is currently being questioned and Mr Sikazwe is being pursued,” Mr Nshinka stated.
Earlier in February, the Department arrested 31 Ethiopians in Nakonde for illegal entry?into the country while in 2009, some Somali youths believed to be victims of an international syndicate involved in human?trafficking, were intercepted.
The illegal immigrants aged between 25 and 40 were?arrested by a combined team of immigration and police officers at?Peulu area on Great East Road.
In the same year, 54 other Ethiopians were each fined K100 each or 20 days simple imprisonment in default.
This was after they pleaded guilty before Kabwe principal resident?magistrate John Mbuzi.
The trend is amidst assurances from Government that it would continue to seal all security?loopholes to ensure illegal immigration is curbed.
Deputy Minister of Home Affairs Stephen Kampyongo said Government is working towards ensuring that this goal is achieved by deploying more security officers to border areas.
Mr Kampyongo also urged members of the public to work closely with relevant authorities to address the challenge.
It certainly creates more questions than answers on what fuels a trend that is sometimes seen as a case of human trafficking or perhaps an illegal ‘exodus’ of foreign nationals for the proverbial greener pastures in other sovereign territorial states.
It has also been established that some illegal immigrants are sometimes in transit to neighbouring countries like South Africa in search of menial jobs with the hope of later graduating to become entrepreneurs.
This trend is significantly under scrutiny by the Immigration Department.
Mr Nshinka expounds that some arrests recorded by the Department in 2014 were due to some foreign nationals entering the country without travelling documents.
He adds that in certain instances, some foreign nationals have found their way into Zambia with the help of smugglers who transport them either to enter or transit through Zambia at a fee.
Zambia is said to be both a destination and a transit point for human trafficking.
“In the recent past, the majority of those intercepted in such a manner have been Ethiopian nationals and to a less extent Somalis,” Mr Nshinka observes.
He says some of those arrested by the department have since been repatriated to their countries of origin.
Mr Nshinka says arrangements with concerned governments to repatriate those still in custody have reached an advanced stage.
“The Department has observed with concern that some people involved in human trafficking have discovered new routes for transporting undocumented persons which makes detection by the conventional mounting of road blocks and check points by security personnel very difficult,” he points out.
“We would like to appeal to members of the public not to relent in reporting any suspicious persons or groups of persons, especially those found in unusual locations and circumstances, to the nearest immigration office,” Mr Nshinka urges.
He says some of the human smugglers are opting to walk over long distances and later get on motor vehicles in places clear of check points to elude immigration and security officers.
Other than Zambia, most Southern African countries are said to be recording many arrests of illegal immigrants, especially from Ethiopia.
According to a report released by the International Organisation for Migration in August 2014, Ethiopia is the main source country for men, women and children trafficked to other countries.
In November 2014, Standard Digital-a Kenyan online publication reported that more than Sh90 million (US$989,100) is illegally earned by human traffickers monthly by smuggling Ethiopians across the Kenya–Ethiopia border with the prospect of sending them by road to South Africa.
Zambia is said to be one of the transit points for human trafficking and illegal immigrants to countries like South Africa.
“On average, 30 Ethiopians allegedly illegally cross the Kenyan border daily in a racket that has been going on for the last 15 years,” Standard Digital states.
This perhaps points to a hint as to why Zambia is having a ‘fair share’ of illegal immigrants and perhaps trafficked humans.

የአማራጭ መኖር ትሩፋት በኤኮኖሚና በፖለቲካ ግርማ ሠይፉ


  • 194
     
    Share
Girma-Seifuዛሬ ስለ አማራጭ መኖር ጥቅም እንዳነሳ የገፋፋኝ በቅርቡ ለቁልቢ ባህል በድሬዳዋ ከተማ ተገኝቼ የተመለከትኩት የቢራ ዋጋ ነው፡፡ ለወትሮ በቁልቢ ሰሞን ብዙም ባይሆን አንድ አንድ ጭማሪዎች ይታዩ ነበር፡፡ በዘንድሮ ግን በአብዛኛው ተጠቃሚ በሚያዘወትራቸው ሆቴሎችና ግሮሰሪዎች “የጃንቦ ድራፍት ዋጋ ዋጋ ብር 6 መሆኑን እናስታውቃለን” የሚል ማስታወቂያ ተመለከትኩ፡፡ ይህ የዋጋ ለውጥ ለምን መጣ ብሎ ሲጠየቅ መልሱ ቀላል ነው፡፡ የአማራጭ ቢራ አቅራቢዎች ወደ ገበያ መግባት ብቻ ሳይሆን፤ በመንግስት ቁጥጥር ስር የነበሩት የቢራ ፋብሪካዎች ወደ ግል ከመዛወራቸው ጎን ለጎን የግል ፋብሪካዎች ቁጥር መጨመሩ ዋነኛው ምክንያት ነው፡፡ እነዚህ የቢራ ፋብሪካዎች፣ ገበያውን ለመቆጣጠር ዋጋቸው ላይ ማስተካከያ ማድረግ ግድ ሆኖባቸዋል፡፡ የተገደዱት መንግስት ባወጣው መመሪያ ሳይሆን ፋብሪካዎቹ እያመረቱት ያለው ምርት አቅርቦት በከፍተኛ ደረጃ መጨመሩ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ በቅርቡ ወደ ገበያ የገባው፤ “ዋሊያ” በመባል መታወቅ የጀመረው ቢራ ፋና ወጊ ነው፡፡ አንድ ጓደኛ “ኢትዮጵያ በምግብ እህል እራሷን ከመቻሏ በፊት በቢራ እራሷን የቻለች ሀገር ነች” ይላል እኔም ይሄን አስተያየት እጋራለሁ፡፡ ለቅንጦት ካልሆነ ቢራ ከውጭ ኢትዮጵያ ማስገባት የግድ ስለማይላት ማለቴ ነው፡፡
እርግጥ ነው በሀገራችን የነፍስ ወከፍ የቢራ ፍጆታ አሁንም አነስተኛ ቢሆንም፣ ከወተት ይልቅ ቢራ በብዛት በገበያ የሚታይባት ሀገር እንደሆነች የእለት ከእለት ህይወታችን ይመሰክራል፡፡ ይህ የአቅርቦት መሻሻል በቢራው ዘርፍ ለውጥ እያመጣ እንደሆነ ቢታመንም ልጆቻችን በሚፈልጉት በወተት መስክም ሊሳካ የማይችልበት አንድም ምክንያት የለም፡፡ ለዚህ ዘርፍ መስፋፋት፣ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሮ ሁሉም በየገበታው ወተት ያገኝ ዘንድ መንግስት ምቹ ፖሊሲና ስትራቴጂ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ ልጆቻችን ወተት እንዲያገኙና ጤናማ ዜጎችን ለማፍራት ከወተት የሚሰበሰብ ታክስ ቢቀርብን ምን ይለናል?
አንባቢዎች ታስታውሳላችሁ ብዬ የምገምተው፤ ስለ የገበያ ውድድር በምክር ቤት ሆኜ ሳነሳ እንደ ምሳሌ የማነሳው ሲሚንቶን ነው፡፡ “ሲሚንቶን የታደገ የነፃ ገበያ፤ ሌሎቹንም እንዲታደግ” በሚል ዘወትር እጠቅሰዋለሁ፡፡ ሁላችሁም እንደምታስታውሱት፤ “ደርባ ሲሚንቶ” ፋብሪካ፣ ወደገበያ ገብቶ የሲሚንቶ ገበያውን እስኪለውጠው ድረስ ቀደም ብለው የነበሩት ሲሚንቶ ፋብሪካዎች የተለያየ ሰበብ እየፈጠሩ ዋጋውን ሲቆልሉት እንደ ነበር ይታወሳል፡፡ እነዚህ ፋብሪካዎች፣ የመንግስት እና የፓርቲ ንብረት እንደ እንደነበሩ ልብ ማለት ይገባል፡፡ ሲሚንቶ ለማምረት የሚያስፈልጉት ግብዓቶች አንዳቸውም በገበያ ላይ ቅናሽ ባላሳዩበት ሁኔታ፤ የአቅርቦት መሻሻል ብቻ በሲሚንቶ ዋጋ ላይ ያመጣውን ከፍተኛ የዋጋ ለውጥ ማንም የሚረዳው ነው፡፡ የሲሚንቶ አቅርቦት ዝቅተኛ በሆነበት ጊዜ ስንቶቹ ለዘረፋ ምቹ ሁኔታ ተፈጥሮላቸው እስከአሁን ድረስ በሙስና ክስ በወህኒ እንደሚገኙም እናውቃለን፡፡ በአቅርቦት ማነስ፣ በሸማቾች ላይ በዋጋ ንረት ከሚደርሰው ጉዳት በተጨማሪ፣ ጥቂቶች ደግሞ በሙስና እንዲጨማለቁ እድል ሰጥቶዋቸው ነበር፡፡ የነፃ ገበያ ስርዓት፣ ብዙ ችግሮችን ሊቀርፍልን ይችላል የሚል እምነት ያለን ለዚህ ነው ፡፡
እንደምታውቁት ብዙ ስኳር ፋብሪካዎች በመንግስት እየተገነቡ ነው፡፡ እነዚህ የስኳር ፋብሪካዎች ተጠናቀው ስራ ሲጀምሩ፣ አሁን በቢራ ላይ መታየት የጀመረው ለውጥ ቀደም ሲልም በሲሚንቶ ያገኘነውን የነፃ ገበያ ትሩፋት ልናገኝ እንችላለን የሚል እምነት የለኝም፡፡ የስኳር ዋጋ ባለበት ከፍተኛ ደረጃ እንዲቀጥል ይደረጋል ብዬ ነው የማምነው፡፡ ይልቁንም በሀገር ውስጥ ምርቱ ትርፍ ቢሆን እንኳ ወደ ውጭ በርካሽ ተልኮ የውጭ ምንዛሬ ማስገኛ ይደረጋል እንጂ፤ ዜጎች በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙት ይደረጋል የሚል እምነት የለኝም፡፡ ምክንያቱም እነዚህ የሚገነቡት ፋብሪካዎች የመንግስት ናቸው፡፡ እነዚህን ፋብሪካዎች የሚመሩት አካላት፣ በምርቱ ላይ ባላቸው ቁጥጥር የተነሳ፤ ምንናአልባትም እንደ ቴሌ “የሚታለብ ላም” ተብሎ ከሚመደቡት ተቋማት እንደ አንዱ ይቆጥሩታል፡፡
በህገ-ወጥ መንገድ ያገኙትን ገቢ አስልተው፣ ትርፍ በትርፍ ሆንን ሊሉን ይችላሉ፡፡ አንባቢ መረዳት ያለበት መንግስት በንግድ ውስጥ ሲገባ፣ በተለይ ደግሞ በዋነኝነት ሲቆጣጠረው ውድድር የሚባለውን ነገር አጥፍቶ በኢኮኖሚክስ፤ “ሞኖፖሊ” የሚባለውን መጥፎ የገበያ ስርዓት ይዘረጋል፡፡ መንግስት ዋና ተግባሩ “ሞኖፖሊ” እንዳይኖር መቆጣጠር መሆኑ ቀርቶ፣ በመንግስት የሚመራ “ሞኖፖሊ” ዘርግቶ ህዝብን ይዘርፋል ማለት ነው፡፡
ከላይ ያነሳኋቸው ነጥቦች በሀገራችን ኢኮኖሚ ውስጥ የነፃ ገበያ በስርዓቱ ቢተገበር፣ ዜጎች ምን ያህል ሊጠቀሙ እንደሚችሉ ጉልህ ማሰያዎች ናቸው ብዬ አምናለሁ፡፡ አማራጭ እና ውድድር ሲኖር፣ ሸማቾች ጥራት ያለው ምርት እንዲያገኙ እድል ይሰጣል ማለት ነው፡፡
በተመሳሳይ፣ በፖለቲካው መስክም መንግስታችን አማራጭ እንዳይኖረን ሰንጎ ይዞናል፡፡ የኢትዮጵያ ሀገራችን የፖለቲካ አልፋና ኦሜጋ፣ “አብዮታዊ ዲሞክራሲ” ብቻ ነው እየተባል ነው፡፡ ለይስሙላ የመድበለ-ፓርቲ ስርዓት እንዲገነባ እንፈልጋለን ቢባልም፣ በተግባር ግን የመድበለ-ፓርቲ ስርዓት የሚፈልጉትን መደላድሎች በማጥበብና በመዝጋት፣ ገዢው ፓርቲና መንግስት የፖለቲካ “ሞኖፖሊ” ለማስፋፋት በቁርጠኝነት ተሰልፈዋል፡፡ ለዚህም የቅርብ ምሣሌ የሚሆነው የመንግስት ስትራቴጂ ለህዝብ ማስጨበጥ በሚል የሽፋን ስም በመላው ሀገሪቱ ዜጎችን በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ለማጥመቅ እየተሄደበት ያለው መንገድ ነው፡፡ እውነቱን ለመናገር ይህ ካለፈው ዓመት ማገባደጃ ጀምሮ በዘመቻ መልክ የአብዮታዊ ዴሞክራሲን በህዝብ ዘንድ ለማስረፅ የተሄደበት መንገድ፣ የህዝብን ሀብት ከማባከን ውጭ የታለመለትን አብዮታዊ ዴሞክራሲ አስተሳሰብን ገዢ የማድረግ ትልም ያሳካ ነው የሚል ግምገማ የለኝም፡፡ ይህ ዜጎችን አማራጭ የማሳጣትና ፖለቲካውን በ “ሞኖፖል” የመያዝ ፍላጎት፣ ዞሮ ዞሮ ይህችን ሀገር አላስፈላጊ አዙሪት ውስጥ ከመክተት ውጪ የተሳካ የፖለቲካ ስርዓት ለመገንባት ያስችላል የሚል እምነት የለኝም፡፡
በግሌ፣ እንደ አንድ ንቁ የፖለቲካ ተሳታፊ ባለፈው የተደረገውን እና አሁን በመደረግ ላይ ያለውን አብዮታዊ ዲሞክራሲን በህዝቡ ውስጥ የማስረፅ እንቅስቃሴ፤ አማራጭ ይዘን የሀገራችን ፖለቲካ ምርጫ ይኑረው ለምንል ዜጎች እንደ አንድ ጥሩ እድል ወስጄዋለሁ፡፡ ገዢው ፓርቲ፣ በመንግስትነት ያለውን መስመር ያለአግባብ ተጠቅሞ የሄደበት መንገድ፣ በቀጣይ ገዢው ፓርቲ ይህን ይመስላል የሚለውን ስራችንን አቅልሎታል፡፡ ቀጣዩ ስራችን የራሳችንን አማራጭ በማቅረብ፣ ህዝቡ ‘ይበጀኛል’ የሚለውን እንዲመርጥ ማድረግ ነው፡፡ ጊዜያችንን ማሳለፍ ያለብን ገዢው ፓርቲ በመንግስትነቱ ለዜጎች ነፃነት፣ ለነፃ የኢኮኖሚ ስርዓት ግንባታ፣ ለህገ-መንግስታዊ ስርዓት መከበር፣ ለህግ የበላይነት፣ ወዘተ የዘጋውን በር እንዴት አድርገን እንደምንከፍተው እና ዜጎች አማራጭ ያላቸው መሆኑን በማስገንዘብ መሆን ይኖርበታል፡፡
በቀጣዩ የ2007 ምርጫ አንድነት ፓርቲ፣ በኢትዮጵያ ውስጥ የኢህአዴግ የፖለቲካ “ሞኖፖሊ” መሰበር አለበት ብሎ ያምናል፡፡ ነገር ግን ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ በአንድ ጊዜ አብዮታዊ ዴሞክራሲን ወግድ ብሎ ሲያበቃ፣ የአንድነትን ሊብራል ዲሞክራሲ ይመርጣል ማለት አይደለም፡፡ ሁለቱም የፖለቲካ አማራጮች ምንናአልባትም ሌሎችም አማራጮች ተጨምረው በፖለቲካ ገበያው ውስጥ ስፍራ ያገኛሉ ማለት ነው፡፡ ዜጎች፣ የተመቻቸውን በመምረጥ ቢያንስ በህገ-መንግስት በግልፅ የተቀመጡትን የመደራጀት፤ ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ፣ በመላው ሀገሪቱ ተንቀሳቅሶ የመስራትና የመኖር፣ ከሁለም በላይ ሀሉም ሰው በህግ ፊት እኩል የሚታይበት ስርዓት ለመዘርጋት፣ ወዘተ.. እድል ይፈጠራል፡፡
ይህ አማራጭ ያለው የፖለቲካ ስርዓት በፖለቲካ ገበያው ውስጥ እንዲኖር ምቹ ሁኔታ መፍጠር የመንግስት ዋነኛ ተግባር እንደሆነ ይታወቃል፡፡ ይህ ሳይሆን ሲቀር እንዲሆን የማድረግ ሀይል ያለው ግን በዜጎች ቁጥጥር ስር ነው፡፡ ዜጎች፣ በሀገራችን በውድድር ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ስርዓት እንዲኖር ቁርጠኛ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡ ለዚሁም ዛሬ ነገ ሳይሉ የመራጭነት ካርድ መውሰድ፤ በምርጫው ዕለት ተገኝቶ ድምፅ መስጠት እና ድምፁን ማስከበር አለባቸው፡፡ ይህ ደግሞ ይቻላል፡፡ የህዝብ ኃይል ከምንም ኃይል በላይ ነው!!!!
ቸር ይግጠመን!!!

የኢትዮጵያ ምርጫ መቆመሪያ ተቋም ገመና – በዳንኤል ተፈራ

የኢትዮጵያ ምርጫ መቆመሪያ ተቋም ገመና – በዳንኤል ተፈራ

  • 1294
     
    Share
10485535_718983234881727_4513979552309356105_n (1)
ያሳለፍነው ሳምንት በሕወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ተሰልተው፣ ታስቦባቸው ይፋ ከተደረጉና አሻንጉሊቱ ምርጫ ቦርድ እንዲፈጽመው በህወሃት ሰዎች ቀጭን ትዕዛዝ ተሰጥቶት ገቢራዊ እንዳደረገው የሚጠረጠረው የፖለቲካ ጉዳይ ይፋ የተደረገበት ነበር፡፡ ይሄው ጉዳይ በአይረቤ ሰበብና በምክንያት አልባ ሁነት ግን ዳግም ከቤተ-መንግስት በወጣ ትዕዛዝ በሚመሰል መልኩ አንድነት እና መኢአድ ወደ ምርጫ ፍክክሩ እንዳይገቡ አይን ያወጣና የሰዎችን የስልጣን ብልግና ባጋለጠ መልኩ መግለጫ የሰጡበት ነው፡፡
እንደዚህ ዓመቱ ምርጫ ቦርዱ የተጋለጠበት ጊዜ አለ ብዬ አላምንም፡፡ ይሄው የምርጫ መቆመሪያ ተቋም እንደ ጫጩት ፍፁም ጠቅላላ ጉባዔ አድርገው የሚያውቁ፣ ቢሮም ሆነ ስራ አስፈፃሚ የሌላቸውን ተቃዋሚ ተብዬዎች በጉያው ሸጉጦ በኢትዮጵያ የመድብለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ላይ እያላገጠ መሆኑ ሳያንስ የገዥውን ፓርቲ ኃላፊነት የጐደለው ተግባር ተቋቁመው ለሃገራችን የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ እየደከሙ ያሉ ፓርቲዎችን እየገፉ ያለበት አግባብ ተቋሙን ከምርጫ መቆመሪያ ማዕከልነት ባለፈ ፋይዳ የሌለው፣ በህወሃት/ኢህአዴግ ማንቁርቱ የታነቀና የራሱ ሳንባ የሌለው ምስኪን ተቋም እንደሆነ ለመገንዘብ ይቻላል፡፡
ይሄው የተጨመደደ ቦርድ ተብየ በኢትዮጵያ ሕዝብ ዘንድ ገለልተኛነቱ አጠራጣሪ ቢሆንም እንደ ሰሞኑ ገለልተኛ አለመሆኑን በይፋ ያረጋገጠበት ወቅት ያለ አይመስለኝም፡፡ የውስጥ አዋቂ ምንጮች እንደሚጠቁሙት ቦርዱ በዋናነት የሚመራው በፕ/ር መርጋ በቃና ሳይሆን በምክትልነት በተቀመጠው የትግራዩ ሰው ዶ/ር አዲሱ ገ/እግዚአብሄር ነው፡፡ ለዚህም ነው በኢህአዴጉ አፈ-ቀላጤ ፍና እና ሌላው ቀላጤ ኢቲቪ በኩል ፓርቲዎችን በህገ ወጥ መንገድ መገፋታቸውን እየገለፀ ያለው፡፡ ሰውየው የቦርዱን ህገ ወጥ ተግባር ህጋዊ አስመስሎ ማቅረብ የሚችል ሰው ነው፡፡ ዶ/ር አዲሱ የፓርቲዎችን የፋይናንስ ክፍፍል ቀመር አዘጋጅቶ ያቀረበ፤ በዚህ ቀመርም በፓርላማ መቀመጫና በክልል ም/ቤት መቀመጫ 55% እንዲይዝ ለማሳመን የጣረ የህወሃት የቁርጥ ቀን ልጅ ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም 55% ጠቅልሎ የሚወሰደው ኢህአዴግ ነው፡፡
ቦርዱ ገለልተኛ አይደለም ስንል እንዲሁ በግብታዊነት ሳይሆን ተጨባጭ መከራከሪያዎችን የማቅረብ አቅም ስላለን ነው፡፡ አንድ ወዳጄ የኢትዮጵያውን ምርጫ ቦርድ በማገዝ ከመቆሪያ ተቋምነት መገላገል እንደሚገባ ስነግረው ተስፉ በቆረጠ ስሜት ግን ደግሞ በምፀት ፈገግ ብሎ “ወዳጄ ቦርዱ እኮ ግንባሩን ከመሰረቱ ፓርቲዎች አምስተኛው ፓርቲ ነው፡፡ የሚያስፈልገው ቦርዱን ማገዝ ሳይሆን አፍርሶ እንደገና መስራት ነው፡፡ በታሪክ ከሚጠየቁ ተቋማት ግንባር ቀደሙ ነው፡፡” ነበር ያለኝ፡፡ እውነትም መፍረስ የሚገባው አይረቤ ተቋም ነው፤ ራሱን ነፃ ያላወጣና የምርጫ መቆመሪያ ተቋም እንደሆነ ግብሩ አረጋገጠ፡፡
አንድነት ፓርቲ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ኢ/ር ግዛቸው በፈቃዳቸው ስልጣናቸውን ከለቀቁ በኋላ አንድነት በመዋቅሩ በአመራርነት የማያውቃቸው ግለሰቦች ተሰባስበው ኢ/ር ግዛቸውን የተካውን አመራር ህግ የጣሰ ለማስመሰል ጥረት ጀመሩ፡፡ የቦርዱ የፖለቲካ ቁማርም ከዚህ ሁነት ይጀምራል፡፡ አንድነትን አስቀድሞ ከምርጫው ለማስቀረት እነዚህን ተራ ግለሰቦች “ጐሽ፣ ጐሽ” ማለት ጀመሩ፡፡ እነዚህ “አንድነት ነን፣ መርህ ይከበር” የሚሉ ጥቂት ግለሰቦች የተንኮል ፖለቲካው አድራሽ ፈርሶች እንጅ በራሳቸው ምንም አይደሉም፡፡ የእነዚህ አፍራሽ ግለሰቦች ያላቸው ብቃት የሚለካው ከኢትዮጵያዊ ጨዋነት ባፈነገጠ መልኩ ለመዋሸት የማይሳቀቁ፤ ተልዕኳቸውን ለመፈፀም አይናቸውን በጨው ያጠቡ የዘመናችን ባንዳዎች መሆናቸው ነው፡፡
ለዚህ ምሳሌ የሚሆነው የመቆመሪያው ተቋም ሳያፍር “አመራር” እያለ የሚጠራው የማነአብ አሰፋ የሚባል የትግራይ ተወላጅ ሲሆን ዕድሜው በሃያዎቹ መጀመሪያ የሚገኝ፣ በተግባሩ ስለሚያፍር በቆብና በጃኬት ራሱን ደብቆ የሚዞር ወጣት ነው፡፡ ይሄ ልጅ አንድነት ቤት ተቀጣሪ ሆኖ ለተወሰኑ ወራት የድርጅት ጉዳይ ተላላኪ ሆኖ ሰርቷል፡፡ አንገት ደፊና አይናፋር በመምሰል የተወነው ትወና አስደናቂ ነው፡፡ የኢህአዴግ ክትትል እንዳላስቀመጠውና ስራ መቀጠር እንኳን እንዳልቻለ እንባ እየተናነቀው ለመናገር የሚችለው ይሄ ወጣት ምርጫ ሲደርስ እንዲፈነዳ ህወሃት አቀባብሎ ያስቀመጠው ፈንጂ እንደሆነ ያወቅነው ቦርዱ “አመራር” እያለ ቢሮው ጐልቶት ስናገኘው ነው፡፡ ወደ ነጥቡ ስንመለስ እነዚህ “አንድነት ነን” የሚሉ በተግባር ግን የአንድነት ወገን ያልሆኑ ስብስቦች ም/ቤቱ በደንቡ መሰረት የተካውን አመራር “ህገ-ወጥ ነው” በማለታቸው ብቻ የምርጫ መቆመሪያው ተቋም በችኮላ አንድ ደብዳቤ ለፓርቲው ፃፈ፡፡ ይሄ የመጀመሪያው ደብዳቤ ኢ/ር ግዛቸውን ፕሬዝዳንት አድርጐ የመረጠውን ጉባኤ ዕውቅና በመንፈግ ዶ/ር ነጋሶን እንደሚያውቅ የሚጠቅስ ነው፡፡ ቦርዱ በችኮላ በየዋህነት የፃፈው ደብዳቤ ለቁማሩ በጆከርነት የሚያገለግሉ ግለሰቦችን ከጨዋታ ውጭ የሚያደርግበት መሆኑን ሲረዳ ምናልባትም አለቃቸው ህወሃት /ኢህአዴግ ለአንድነት ቦርድ የፃፈውን ዝርዝር ደብዳቤ ሲመለከት ለሴራ ፖለቲካ እንደማይመች ሲረዳ በአስቸኳይ ቀይር ብሎት ይመስለኛል፡- “እሱን ደብዳቤ ተውት” ከሚል መልዕክት ጋር ሌላ 3 ነጥቦችን የያዘ ደብዳቤ ላከ፡፡
የመጀመሪያውን ደብዳቤ ተውት ያለበት ምክንያት ለአፍራሽ ተልዕኮ የተዘጋጁ ገልቱ ግለሰቦች ከጨዋታ ውጭ ስለሚሆኑ ነው፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ግለሰቦች በዶ/ር ነጋሶ የአመራር ዘመን አይታወቁም ወይም የሉም ነበርና፡፡ ባለ ሦስቱ ነጥብ ደብዳቤ ሲመጣ ግን አንድነት የፖለቲካ ዕደንድምታውን በጥንቃቄ ገምግሟል፡፡ ምነው ቢሉ ይሄ ከቦርዱ በስተጀርባ የሚደንስ አካል እንዳለ በመረጋገጡ ነው፡፡ ዳንሰኞቹ ምርጫን ለማስመሰያና ማወናበጃ እንጅ በትክክል ሊጠቀሙበት አይፈልጉም፡፡
የደብዳቤው ሦስት ነጥቦች የሚከተሉት ነበሩ አንደኛው ም/ቤቱ የጠቅላላ ጉባኤ ውክልና እንዳለውና ም/ቤቱ ፕሬዘዳንት መምረጥ እንደሚችል አብራሩ፤ ሁለተኛው የጠ/ጉባኤ ሪፖርት በጊዜ አስገቡና የመጨረሻው የጠቅላላ ጉባኤ የኮረም ቁጥር ግለጹልን የሚል ነበር፡፡ በጣም ቀላልና ተራ ጥያቄ የሚመስል ነበር፡፡ አንድነት በፍጥነት ምላሽ ሰጠ፡፡ የመቆመሪያው ተቋምም የሰጠነውን ምላሽ “በቅንነት” እንደተቀበለው ገልጾ ነገር ግን የጠ/ጉባኤ ቁጥር በደንቡ እንድናካትት የሚጠይቅ ደብዳቤ ፃፈ፡፡ በቅንነት የምትለውን ግን በቅንነት አልተመለከትነውም፡፡ ጉባኤ በፍጥነት መጠራት እንዳለበትና ምርጫ ቦርዱ የጠየቀውን አሟልተን በሙሉ ልብ ወደ ምርጫ መግባት እንደሚገባ በመታመኑ በሳምንት ጊዜ ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ የምርጫ ቦርድ ተወካይ ባለበት በስኬት ተጠናቀቀ፡፡
አንድነትም ገዥዎች ባዳፈኑት የፖለቲካ ምህዳር እና ልፍስፍሱ ቦርድ ቢኖርም ህዝቡን አንቀሳቅሽ በ2007 ዓ.ም የአምባገነኑ ስርዓት ፍፃሜ ይሆናል በሚል ፅኑ እምነት ሙሉ ለሙሉ በስራ ተጠመደ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜም የህዝብ ታዛቢዎችን ምርጫ በመላ ሀገሪቱ ያሉ ቢሮዎቹን በመዝጋት በንቃት ተከታተለ አጋለጠ፡፡ ህዝቡ የምርጫ ካርድ የሚወስድበትንና በካርዱ ለመጀመሪያ ጊዜ አሸናፊ የሚሆንበትን ስትራቴጂ መንደፍንና ሕዝባዊ ንቅናቄ እንደሚያስፈልግ ይፋ ማድረጉ ተከትሎ የ40 እና 50 ዓመት የመግዛት ህልም ያላቸው “ነፃ አውጭዎች” መንደር ጫጫታና ጭንቀት ፈጠረ፡፡
ይህንን ጭንቀት ለማርገብ አንድነትን ከምርጫ ጫወታ ማስወጣት እንደሚገባ ታመነበት፡፡ ለዚህ ማስፈፀሚያ የመቆመሪያው ተቋም አለ፡፡ በጠቅላላ ጉባኤው ተወካዩን የላከው ቦርዱ ሌላ ታሪካዊ ስህተት ለመስራት ደፈረ፡፡ ከቦርዱ በስተጀርባ ያሉ ዳንሰኞች ማንቁርቱን ስላነቁት ምርጫ አልነበረውም፡፡ ይሄ ተራ ጨዋታ በፋና እና ኢቲቪ ታጅቦ ለህዝብ ቀረ፡፡ ድራማው “የውስጥ ችግሮቻቸውን ካልፈቱ ወደ ምርጫ አይገቡም” የሚል ነው፡፡ የውስጥ ችግር ከማን ጋር? እንዴት? መልስ የላቸውም፡፡ ኢ/ር ግዛቸው በፈቃዳቸው ለቀው ወደ ግል ጉዳያቸው ገብተዋል፡፡ ታዲያ እነዚህ አመራር ተብየዎች እነማን ናቸው? እነዚህ የአንድነት አመራር እንዲደራደራቸውና ችግሩን እንዲፈታ የተጠየቁት ግለሰቦች በፓርቲው የአመራር መዋቅር የማይታወቁ፤ ከየመንገዱ ተለቃቅመው የመጡ ተራ ሰዎች ናቸው፡፡
ህወሃት/ኢህአዴግ በቦርዱ በኩል ይህንን ተራ ድራማ እየሰራ ያለው አንድነት ወደ ምርጫ እንዳይገባ ለመከልከል የወሰነው የፖለቲካ ውሳኔ ስጋ ለማልበስ ነው፡፡ የእርኩም ስጋ፡፡ ሁሉም በሰፈረው ቁና የሚሰፈርበት ቀን እንደሚመጣ ቅንጣት አልጠራጠርም፡፡ እየተካሄደ ያለው ሰላማዊ ትግል ከዚህ ዓይነት ተራ ድራማ በላይም ነው፡፡ ትግሉ የነፃነት የመውጣትና ተደፍቆ የመኖር ነው፡፡ ወደ ምርጫ እንገባለን ስንላቸው በዚህ ደረጃ ተርበትብተዋል፡፡ ምርጫ ቦርድም ያለውድድር ለኢህአዴግ ተጨማሪ የአገዛዝ ዘመን ለመስጠት ዝግጅቱን የጨረሰ ይመስላል፡፡ ይሄ የስርዓቱን የውድቀት ፖለቲካ የሚያሳይ ነው፡፡ የዚች ሀገር ትግል የቦርድ ወይም የሌላ ትግል አይደለም፡፡ ትግሉ በሕዝቡ እጅ ላይ የወደቀበት ታሪካዊ ወቅት ነው፡፡ ታሪካዊ ጊዜ ዴሞክራሲን እናሰፍናለን የሚሉ ሰዎች በግብራቸው ያፈሩበት ታሪክ፡፡ ይህንን በአደባባይ ቆመን የምንናገርበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም፡፡
2007 ለለውጥ!!!