Monday, March 30, 2015

**ድንቄም ምርጫ**

ፍትሕ በተረገጠበትና የዴሞክራሲታዊ ሥርዓት በኃይል በታፈነበት አገር ሕዝብ መሪውን መምረጥ አይችልም።
              EPRDF Election1የምርጫ ጉዳይ ሲነሳ ወደ ኋላ ሄደን የዘመነ ኃይለሥላሴን፤የደርግን የምርጫ ሂደቶች ብናስብ ከዚህ በሰለጠነው ዓለም ከሚካሄደው ምርጫ ጋር በምንም ሁኔታ ሊመሳሰል እንደማይችል ሁላችንም ግልጽ የምንሆን ይመስለኛል።አድሎአዊና ሕዝብን ያላሳተፈ የገዥው መደብ የሚፈልጋቸውን እጩዎች መልምሎ በማቅረብ ሕዝቡን አስገድዶ እንዲመርጣቸው ማድረግ አይነተኛ ባሕሪው መሆኑን መጠራጠር አይኖርብንም።
የባሰ አለ እንዲሉ ከአንድ መንደር የተሰባሰቡና በዘረኝነት በሽታ የተመረዙት (ጎሰኞች) የአሁኖቹ ገዥዎቻችን ከ1997 ምርጫ በፊት ከምርጫው በፊትና በምርጫ ወቅት ሲፈጸም የነበረውን ሤራ በሚገባ የማውቀው ሲሆን የተቃዋሚ ኃይሎች(ድርጅቶች)ውስብስቡን የካድሬ መሰናክል አልፈው በፓርላማው ውስጥ ጥቂት አባሎቻቸውን በፓርላማ ውስጥ እንዲገቡ ያደርጉ ነበር።በፓርላማው ውስጥ ሃሳባቸውን የመግለጽና የማራመድ እድላቸው የጠበበ ቢሆንም የፓርላማውን ውሳኔ የሚነቅፍ የተቃውሞ ድምጽና የተአቅቦ ድምጽ ማስቆጠር ችለው ነበር።ከ1997 ምርጫ በኋላ ግን ዘረኝነት መራሹ ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ(ህወሃት)ከኢትዮጵያ ሕዝብ ተነጥሎ እንደቆመ ተንሳፎ የሚገኝ መሆኑን ሕዝብ በምርጫ ካርዱ ፍርዱን ሲሰጥ የበረገገው ገዥ ቡድን ረጅም እጁን የምርጫ ኮሮጆ ዘረፋ ውስጥ አስገባ ያልተመረጠውን ተመርጫለሁ አለ።ሰርቀሃል ድምጻችን መልስ ሲባል ደግሞ ግድያ፤እስራት፤ስብሰባ መከልከል፤ሰላማዊ ሰልፍ የማይደረግ መሆኑን አወጀ በግብርም ውሎ አየነው።ከዚያ በኋላ የዚህን ትውልድ አምክን ዘረኛ አገዛዝ እድሜ ለማስረዘም የደህንነት፤የመከላከያ፤የፖሊስና የልዩ ፖሊስ የክልል ፈጥኖ ደራሽ፤የካድሬው መዋቅር ትኩረት ተሰጥቶ እንዲጠናከር ተደረገ።አፈናው ግድያው ተስፋፍቶ ኢትዮጵያውያን በየጎዳናው ወድቀው የሚገኙበት ሁኔታ ተፈጠረ።
woyaneይህ የምታዩት የህወሃት መለያ ሲሆን ከብጫው ላይ የተቀመጠው ዓርማ የጀርመን ናዚ ልዩ ምልክት የነበረ ሲሆን ዛሬ ኢትዮጵያውያን ህወሃትን ሲያነሱ የጀርመን ናዚን የጀርመን ናዚን ሲያነሱ ህወሃትን የሚያስታውሱበት ምክንያት ህወሃትና የጀርመን ናዚ በቆዳ ቀለም ቢለያዩም በተግባር አንድ ናቸው ብለው ስለሚያምኑ ነው። እኔ የዚህ ጹሑፍ አቅራቢም ህወሃትን ከጣሊያንና ጀርመን ፋሽስቶች ለይቸ አይደለም የምመለከተው።ለዚህ ጹሑፌ መነሻ የሆነኝ የፊታችን ግንቦት ለሚካሄደው ብሔራዊ ምርጫ የህወሃትን ሥርአት በሰላማዊ መንገድ ታግለን በምርጫ አቸንፈን ሥልጣን እንጨብጣለን ብለው በተነሱ ኃይሎች ላይ የህወሃት የምርጫ ቦርድ የፈጸመውን አሳፋሪ ድርጊት ተመልክቸ ሲሆን በምንም አይነት መስፈርያ ይሁን የተቃዋሚ ኃይሎች ለምርጫ ውድድር የሚያቀርቡትን እጩ ራሳቸው ወስነው ያቀርባሉ እንጅ የምርጫ ቦርድ ይህ ይመረጥ ይኸኛው አይመረጥ ብሎ የመወሰን ሞራሉም ሆነ ብቃት የለውም።ለዚያውም በእጣ! የምርጫ ኮሮጆ ገልብጦ ያልተመረጠውንና ሕዝብ አንቅሮ የተፈውን ተመርጠሃል ሕዝብ ይሆነኛል ያለውን በምርጫ ያቸነፈውን አልተመረጥክም ብሎ የሚቀጥፍ የአንድ ሥርአት አገልጋይና ተቋም አምኖ ምን አይነት ምርጫ እንደሚካሄድ ከወዲሁ መተንበዩ ነብይ የሚያሰኝ አይደለም።ለሥርአቱ አስጊ የሆኑ የተቃዋሚ ድርጅቶችን አንድነትና መኢአድን በኃይል አፍርሶ የየድርጅችን ንብረት ዘርፎ በሌሎቹ የተቃዋሚ ኃይሎች ጉያም ለመግባት ረጅሙን ዘራፊ እጁን ለማስገባት እያሴረ ያለው ህወሃትና ጉዳይ አስፈጻሚው የምርጫ ቦርድ ሕገ-መንግሥቱን እየናዱ መሆኑን ሊያጤኑ ይገባቸዋል።
ህወሃት መሠረታዊ ችግሩ ድህነት ከሆነ በትግራይ ሕዝብም ይህ ችግር እንደ ዋነኛ ተደርጎ ከተወሰደ ሌሎችስ ብሎ ማሰብ የሚችል ተፈጥሮ በህወሃት ቤት እንዳማይኖር ቢታወቅም በትግራይ ለተፈጠረው የኢኮኖሚ መዳከምም ሆነ የንዋይ ጥማት የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚጠየቅበት አንዳችም ምክንያት ሊኖር አይገባውም የህወሃት መራሹ ቡድን በፈጠራ ውሸት የቆጥ የባጡን በመቀባጠር የሕዝብ እልቂት እንዲፈጠር በማድረግ በውንድብድና የካሄደው ዘረፋ፤ዜጎችን በተለይም ምሁሩንና አምራቹን ኃይል ከሀገር መንቀልና የመራሹ ቡድን እንባ ጠባቂዎችና ቤተሰቦች አገሪቱን ተስፋፍተው እንዲይዙና ሌላው ዜጋ በዘመናዊ ባርነት መቀጠል ወይም በሌሎች ላይ የደረሰው ጽዋ ሞልቶ እንዲፈስበት ማድረጉ የሚያስከትለውን መዘዝ መገንዘብ ባለመቻል የተፈፀመ ስለሆነ የዛሬው እዩኝ እዩኝ ነገ ሸሽጉኝ ሸሽጉኝን እንደሚያስከትል በድፍረት መናገር ይቻላል።
በአንድ ወቅት የህወሃቱ ፊታውራሪ ስብሃት ነጋ ከጋዜጠኛ ለቀረበለት ጥያቄ ሲመልስ፡) እንዲህ ብሎ ነበር-ጋዜጠኛ አቶ ስብሃት ድሮ የሃብታምና የባለሥልጣን ልጅ ነበር ስኮላር ሽፕና የውጭ ትምህርት እድል ያገኝ የነበረው ዛሬ ደግሞ የእናንተ ልጆች የሚማሩት ወደ ውጭ አገር ሄደው ነው ሲባል(፡ አቶ ስብሃት ታዲያ እነሱ ያደረጉትን እኛ ብናደርገው ነውሩ ከምኑ ላይ ነው ብሎ ነበር በአራት ነጥብ የዘጋው።እንግዲህ ህወሃት እንዲህ ያሉትን ውዳቂዎችንና ፀረ-ሕዝቦችን አቅፎ ነው ኢትዮጵያን በኃይል አንበርክከን እንገዛታለን ካልሆነልን ደግሞ እናፈራርሳታልን የሚሉን።ከዚህ ወዲያ እብደት የለም እንዲህ ያሉት እብዶች የተሰባሰቡበት ህወሃት ነው ዛሬ በትረ ሥልጣኑን ጨብጦ እየገዛ ያለው።
አንዱ በአንዱ ላይ እምነት እንዳያሳድርና በጥርጣሬ እንዲተያይ ጦርነት ውስጥ እንዲገባ፤አንተ የዚህ አንተኛው ደግሞ የዚህኛው ዘር ነህ በማለት በዘር በማናከስ የሕዝብ ሰላም እንዲደፈርስ ያደረገው ህወሃት ነው። ሰሞኑን ደግሞ አንድ አስገራሚ ድርጊት ተፈፀመ ይህኸውም(ጥቂት ህወሃት የመለመላቸው የቅማንት  ተወላጆች ) በአማራ ገዥ መደብ እስከ ዛሬ ተገዝተናል አሁን በቃን ጐንደር የቅማንት አገር ስለሆነ ራሳችን በራሳችን ለማስተዳደር እንድንችል የራስ ገዝ አስተዳደር ይገባናል በሚል ሲንቀሳቀሱ ቆይተው አሁን የነአቶ በረከትና አዲሱ ለገሠን ይሁንታ አግኝተው ያልተጻፈ የታሪክ ድሪቶ አንግበው በደምና በስጋ የተቀላቀላቸው ወገናቸው ጋር ደም የሚያፋሥስ መንገድ መጀመራቸው ቀልጥፈው ተግባራቸው እኩይ ተግባር መሆኑን አውቀው እንዲያቆሙት ለማስገንዘብ ነው ይህን ጹሑፍ ያዘጋጀሁት። በዚህ ተግባር ግንባር ቀደም ሆነው የሚያራምዱትን በአካል ስለማውቃቸውም ጭምር ወንድማዊ ምክሬን ሊሰሙ እንደሚችሉ በማመን ነው። ህወሃትና የአማራውን ህዝብ ጋንጃ እየመታ የሚገኘውን ብ.አ.ዴ.ንን አምኖ ወደዚህ አጣብቂኝ ጉዳይ መግባት በፍጹም ስህተት ነው።የቅማንት ተወላጅ ለህወሃት የምርጫ ፍጆታ መዋል የለበትም፦የህወሃት ሥርዓትና የሥርአቱ አራማጆች መቀበሪያቸውን ቆፍረው ከመቃብር አፋፍ ላይ በሚገኙበት ወቅት መልካም ታሪክን ማጉደፍ አይገባም።ይህ ስርዓት ወዳቂ ነው በሀገር ጥፋትና እጁን በደም የነከረ ሁሉ በሰፈረው እንደሚሰፈርም ግልጽ ነው።ነገ የዛሬዎቹ ዳኞችና እኛ ፊት ለፊት እንገናኛለን፤ ነገ እኛና ይህወሃት ካድሬ እንገናኛለን፤ነገ የምርጫ ቦርድና እኛ እንገናኛለን፤ነገ የፌደራል ፖሊስና እኛ እንገናኛለን፤ነገ እኛና ፖሊስ እንገናኛለን፤ነገ የአጋዚ ሠራዊትና እኛ እንገናኛለን፤ነገ እኛና የክልል ፈጥኖ ደራሽ እንገናኛለን፤ለዘመናዊ ባርነት ወደ ዐረብ አገር የተላኩ እምቦቃቅላ ሴትና ወንድ ወጣቶችን መዝግበናል፤አገር ጥለው እንዲወጡ የተገደዱ ሙራንና ጋዜጠኞችን ዝርዝር ይዘናል፤ወህኒ ቤት ወርደው ሌትና ቀን እንደ እባብ እየተቀጠቀጡ የሚገኙትን ወጣት ጋዜጠኞችና የፖለቲካ ድርጅት አመራሮችን እናውቃቸዋለን፤በመላ ኢትዮጵያ የመኖርና ሠርቶ የመብላት መብት የተነፈገው ዘሩ በመድሃኒት እንዲመክን የተደረገውን የአማራ ነገድ ሕዝብ ጉዳይ በሚገባ ተመዝግቦ እንዲቀመጥ ተደርጓል፤ከወሎና ጎንደር ተነጥቆ ወደ ትግራይ የሄደውን መሬት በሚገባ እናውቀዋለን ይህን ሁሉ ህወሃትና መንገድ መሪዎቹ የሚከፍሉት እዳ እንደሆነ ሊያውቁት ይገባል። በዚህ አጋጣሚ አቶ በየነ አስማረና አበበ ንጋቱን አመስግኘ ማለፍ እወዳለሁ።« በወደቀ ግንድ ምሳር ይበዛበታል እንዲሉ » ጣሊያን ጎንደር ሲገባ የተጠቀመበትን ፕሮፓጋንዳ ያነገበው የህወሃት ቡድን ኢትዮጵያን ለመበታተን ሲል የሚያራምደውን የጎሳ ፖለቲካ የተጋቱ አውቆ አጥፊ የቅማንት ተወላጆችንና ሌሎች የተለያዩ በአማራው ነገድ ህዝብ ክልል የሚኖሩ ጎሳዎችን በማነሳሳት በጎሳ መራሹ ቡድን ጣቱን የቀሰረውን ሕዝብ አስተሳሰብና አመለካከት አቅጣጫውን እንዲስት ለማድረግ የሚጠቀምበትን ሕዝብን በሕዝብ የማናከስ ሤራ እያራመዱ ይገኛሉ።
24 ዓመት በመድፈን ላይ የሚገኘው የህወሃት አገዛዝ በሚያካሂዳቸው ምርጫዎች አንድም ቀን ፍትሃዊነት ያልታየበትና የተጭበረበረ መሆኑ እንዳለ ሆኖ በምርጫ ወቅት ለሕዝብ የሚገባቸውን ቃሎች ከመካዱ አልፎ በተቃራኒው እንደሚተገብራቸው ይታወቃል።የዘንድሮ ደግሞ በጣም የለየለትና አውሬነቱን በግልጽ የሳየበት ሁኔታ ላይ ደርሷል ሁላችንም የምግባባበት አንድ መሠረታዊ ጉዳይ ህወሃት ለአፍታም ቢሆን ሥልጣን ከእጁ ካፈተለከ የሚደርስበትንና የሚከፍለውን ዋጋ ስለሚያውቅ በሰላማዊ መንገድ ሥልጣን ያስረክባል ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ዋናው አነጋጋሪ ጉዳይ ሕዝብ ካለፈው ተመክሮ የማያገኘውና አልመርጥም የማይልበት ምክንያት ምንድን ነው የሚለው ይሆናል።የሚያሰድድን፤የሚገድልን፤አስሮ የሚያሰቃይን፤ዘር በማጥፋት ላይ የተሰማራን ነብሰ-ገዳይ ቡድንን መርጦ በሥልጣን ላይ ማስቀመጥ አገርን ከመገደል የከፋ ወንጀል ነው።ስለዚህ ሕዝቡ የዘንድሮውን ምርጫ በእምብይታ ሊያስተናግደው ይገባል።

Saturday, March 28, 2015

Fallacious Election of Ethiopia and Its Disasters

In most parts of our modern world democratic governments hold free, fair and regular or periodic elections to improve the administration system in their countries, thereby guaranteeing citizens the opportunity to change their leaders and to support new policies. Non democratic regimes, like a government of Ethiopia hold regular election but citizens are systematically forced in different ways to vote for them. Democratophobic government of Ethiopia holds regular and symbolic election in the name of democracy to learn new suppression techniques and to identify its supporters from non supporters. An identification of its allies along with the newly gained knowledge or technique from election will help the regime effectively to suppress critic voices and monopolize the country’s political or government power under its arms in future ruling years. Woyane of ‘Z Tigray’ regime hold periodic election not democratically to transfer government power and political authority into the hands of popularly elected or winner party but uses periodic election as instrument periodically to terrorize citizens of the country. The terrible consequences of Ethiopian elections are violations of democratic and human rights, cause of deaths for many and mass arrest. In Ethiopia elections or peaceful forms political struggles have never brought any limit to the power of ruling government, improvement in human rights situation or reform in government’s administration system. It had gone from bad to worse and from worse to worst.
The TPLF of Ethiopia symbolically holds periodic election every five years and the so-called constitution states that electoral institution to be free from any sort of government influence. However the electoral institute is not only influenced, nevertheless since its establishment it served as the survival gear of the ruling government. Article 102 of the constitution states independence of national election board to conduct in an impartial manner free and fair election in federal and state constituencies. It continues to state again that members of the board shall be appointed by the HPR upon recommendation of the prime minister. Here we can observe that the first part statement of the article clearly contradicts with the concept or notion of the second section. The first part of Article 102 tells us the election boards shall be independent and free from any form of influence. On the other hand, the second subdivision says the election boards shall be recommended by the prime minster and then later on elected by the votes of house of HPR. The prime minister is in charge of recommending his/her trusted friends or loyalists who are willing to execute whatever is ordered. The process of nomination and establishment of election board is just an appointment of the loyalists to certain position in separate suppression institute inside the circle of TPLF. The appointed officials are directly influenced by prime minster or other higher governmental bodies. This makes the country’s electoral system and process, electoral computations and vote results partial and biased. The contest and winning rooms for opposition parties are limited as well as votes are rigged by the electoral board since the election board is directly established by the Government to serve the will of government not to execute election and its process fairly. The malfunction of electoral board is an open threat to build democratic system.
In addition to the influence of National Election Board on the opposition parties and the outcome of election results, the harassment, assault, false accusation and imprisonment, severe restriction on freedom of speech, intolerance to open discussion and other negative influences of government hinders oppositionists from effective electoral computation. Oppositionists lack resources and budgets for their awareness creating campaign in nearest or most remote areas of the country. In reality power hungry TPLF doesn’t want efficacious computations of the opposition parties as result it holds back resources or finances which are allocated for the opposition political parties. Also there is campaign finance abuse by TPLF and agents, dependent electoral board and no balanced access to the media for all opposition political parties and candidates.
During the campaigns for election the importance of freedom expression is undisputable. Individuals should express their will and political opinions freely, take part in campaigning and at end elect the party that they choose and trust. In contrast, the TPLF regime has severely restricted freedom of expression and opinion, association and peaceful assembly of individuals, groups and organizations. This makes a tremendous roadblock for opposition political organizations to create awareness for public about their mission, vision and policies. Lack of open public discussion reduces the participation of citizens in their country’s socio-political affairs which in turn affects democracy building process according to an accepted international election standards and rules. In fact there exist electoral law to make the election peaceful, free, fair and democratic on the paper. But these laws are interpreted in the way they are convenient to keep the interests of TPLF. The so called Electoral Law of Ethiopia bears the following code of conduct of election and objectives. Let’s consider realities on the ground and the stated law as follow
1. To promote tolerance in a democratic electoral operation; under no circumstances TPLF and its system has tolerance in electoral process or in opposition opinions. TPLF never promoted tolerance either democracy instead every single opposition voices are systematically and openly suppressed. TPLF shoulders are not able to carry any political opinion that goes against them.
2. To foster free political campaigning and open public discussion; so far no opposition political groups had any free campaigning. Most opposition parties’ leaders and campaigners were humiliated attacked in Gondar, Wolayta, Oromia, in the capital Addis Ababa and many other parts of Ethiopia. No opposition political party is allowed holding open public discussion. The ruling minority junta is scared of allowing open public discussion. Also in the country where freedom of speech is severely restricted, it is impossible to hold open public discussion. Woyane knows well its fate, if open public discussion is held.
3. To enable the conduct of free and fair election. On this section it says any political organization including TPLF itself or private candidate must therefore respect, publicize, educate the electors and guide its candidates, representatives and supporters to respect the code and take necessary actions to realize it. But none of the listed codes are respected by the TPLF of Z Tigray and these laws are simply written on the paper to fool or attract foreign donors and to establish symbolic opposition parties which are not allowed to go beyond the stated limit.
In general the hope of removing Woyane of Z Tigray from government power and democratically transferring political power in to the hands winner political party is impossible from palpable evidence of Ethiopia’s political situation. This cumulative reason brings us to the conclusion that the outcome of Ethiopian election is predetermined. The above listed methodical fortification, open and hidden barriers are all the techniques which TPLF use to hold back opposition political organizations from effective electoral computation before election. At the time of election processing an illegal interference of TPLF government in the process of election such as vote counting and publicizing the election result is clear in addition to electoral board frauds. Both the governments’ illegal interference and election board dishonesty makes the electoral fraud to be outlawed jointly by the government and electoral body or legislation. The electoral fraud of Ethiopia includes the fabrication of electoral results, increasing the vote share of TPLF and reducing or weighing down the vote share of opposition parties.
Shortly after symbolic TPLF election ends post election terrorization of oppositionists and non allies of government starts. Government targets defenseless non-supporters, opposition parties (leaders, members and institution) and anybody who criticizes the system. Those who are found to be anti-TPLF coalition government or being in connection with opposition political parties will suspended or sacked from their jobs, dismissed from their positions, denied access to employment or other opportunities and in most cases systematically persecuted and sentenced years of imprisonment. For instance an iconic Ethiopian politician and opposition political leader Anduale Aragie was one of the victims of post election persecution by the government. Another citation is post election crackdown of government in 2005 in capital Addis Ababa during peaceful protest of the voters. The peaceful rally was interrupted by police brutality which led to death of hundreds of innocent and arrest of 1000s including figure opposition political leaders. Election 2005 was the event that led TPLF to devise a new suppression strategy to control powerful opposition politicians, journalists and political activists. After a few years later TPLF introduced the so-called anti-terrorism law to hunt down any dissents. Anti terrorism legislation enabled TPLF to arrest famous opposition figures, journalist, human rights activists and others. These Ethiopians were persecuted and imprisoned for no crime but only for holding different political opinion and view.
TPLF regime has made evident the notion that elections alone cannot establish and bring democracy in Ethiopia. To build democratic system and establish strong democratic institution in Ethiopia it is essential to remove Woyane by armed struggle either through public disobedience and all other possible ways. Without democracy’s other essential elements such as consent of the governed, constitutional limits, the protection of human, minority and democratic rights, accountability and transparency, a multiple party system, economic freedom and the rule of law elections alone cannot guarantee the freedom and democracy. It is well known that the democratic institutions in Ethiopia are very weak and elections are easily used by violent and dictator regime to monopolize government power for life long. Therefore it is essential to create unified web like network of opposition outside and inside the country by using all available measures and techniques to bring an end to long-standing dictator regime of Ethiopia.

Tuesday, March 24, 2015

ጎንደር ዝምታውን ሰብሯል – የመከላከያ ሰራዊት አባላት በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ታዘዋል

መጋቢት ፲፬(አስራ አራት) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ሰሞኑን በሰሜን ጎንደር አካባቢ የታየውን የጸጥታ መደፍረስ ተከትሎ የአገሪቱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት ካለፈው ሃሙስ ቀን ጀምሮ በተጠንቀቅ እንዲቆሙ ታዛዋል።Ethiopian soldiers in Barentu
የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት የአየር ሃይል አባላት ካለፈው ሃሙስ ጀምሮ ከግቢ እንዳይወጡ ሲታዘዙ የተወሰኑት ደግሞ ከደብረዘይት እና ድሬዳዋ አየር ሃይል  ወደ መቀሌ አምርተዋል። ብዛት ያለው የእግረኛ ሰራዊትም ወደ ኤርትራና ሱዳን ድንበሮች አቅንቷል።
ወታደራዊ ልምምዶችና አዳዳስ ምልመላዎችም እየተካሄዱ መሆኑንም ምንጮች ገልጸዋል።
ማንነታቸው በውል ያልታወቀ የተቃዋሚ ሃይሎች ጎንደር ከተማ ውስጥ የሚሊሺያ አዛዥ የሆነውን ኮማንደር ተፈራን ገድለው  ካመለጡ በሁዋላ፣ እነሱን ለመያዝ መጋቢት 12 አርማጭ ልዩ ቦታው እንኮይ ተራራ ላይ በተደረገ ጦርነት ፣ ከተቃዋሚዎች በኩል ሻምበል ይርዳውና
አዲሱ የተባሉ  ሲገደሉ፣ ከመንግስት ታጣቂዎች በኩል ደግሞ  የልዩ ሃይል አባል የሆነው  እባበይ እንዲሁም አንድ ስሙ በውል ያልታወቀና ሁለት የሚሊሺያ አባላት ተገድለዋል። ከቀኑ ዘጠኝ ሰአት ጀምሮ እስከ ምሽት በቀጠለው የተኩስ ልውውጥ፣ አንድ ተማሪ በመንግስት
ሃይሎች ተገድሏል። የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች ምሽት ላይ አካባቢውን ጥለው መውጣታቸውን የአይን እማኞች ገልጸዋል።
በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስትን አስተያየት ለማካተት የተደረገው ጥረት አልተሳካም።

አርበኞች ግንቦት7 – ህዳሴም ሆነ ዉዳሴ ክህዝብ የሚደበቅ ምንም ነገር የለም!

March 24, 2015
Patriotic Ginbot 7 Movement for Unity and Democracyከሰሞኑ አገራችን ኢትዮጵያን በተለይም ብሄራዊ ጥቅሟንና ደህንነቷን በተመለከተ ሁለት አቢይ ዜናዎች የአገራቸን የኢትዮጵያንና የኢትዮጵያ ጉዳዮች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚመለከታቸዉን አገሮች የአየር ሞገደች ተቆጣጥረዉት ነበር። ከእነዚህ ዜናዎች ዉስጥ አንዱና ዋነኛዉ ኢትዮጵያ፤ ሱዳንና ግብፅ የህዳሴዉን ግድብ አስመልክቶ ስምምነት ላይ ደረሱ የሚል ዜና ሲሆን ሁለተኛዉ ደግሞ አለም አቀፍ ጋዜጠኞች የህዳሴዉ ግድብ የሚሰራበት ቦታ ድረስ ሄደዉ ባካሄዱት ጥናት መሠረት የህዳሴዉ ግድብ ፕሮጀክት ባጋጠመዉ ከፍተኛ የገንዘብ እጥረት የተነሳ እንዲዘገይ መወሰኑን የሚያወሳ ዜና ነዉ። አርበኞች ግንቦት ሰባት ለአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ኢትዮጵያ ዉስጥ ለሚሰሩ ምንም አይነት ስራዎችና በኢትዮጵያ ህዝብ ስም ከየትኛዉም አገር መንግስትና መንግስታዊ ካልሆነ ተቋም ጋር ለሚደረጉ ስምምነቶችና ዉሎች ሁሉ ባለቤቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ነዉ ብሎ ያምናል፤ ስለሆነም አርበኞች ግንቦት ሰባት የኢትዮጵያን ህዝብ ብሄራዊ ጥቅምና ደህንነት ከሚመለከቱና በሚስጢር መጠበቅ አለባቸዉ ተብሎ ከሚታመኑ አንዳንድ ጉዳዮች ዉጭ ሌላ ምንም ስራ ወይም አለም አቀፍ ስምምነትና ዉል የኢትዮጵያ ህዝብ ሳያዉቀዉና ሳይሰማዉ በድብቅ መደረግ የለበትም የሚል የጸና እምነት አለዉ። ሆኖም ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ አገዛዝ ኢትዮጵያን ከቅኝ ገዢዎች በከፋ መልኩ የሚገዛ የጥቁር ፋሺስቶች አገዛዝ በመሆኑ የሚሰራቸዉ ስራዎችና በአለም አቀፍ ደረጃ የሚፈርማቸዉ ዉሎችና ስምምነቶች የኢትዮጵያን ህዝብ ብሄራዊ ጥቅም የሚጻረሩና የሚጋፉ ድብቅ ስምምነቶች ናቸዉ።
ይህ የወያኔ መሪዎች ከኢትዮጵያ ህዝብ ጀርባ ላይ ተሸሽገዉ የሚሸርቡት የድብብቆሽ ሴራ ዛሬ የተጀመረ አዲስ ክስተት አይደለም። ባለራዕዩ መሪ የሚል አላስፈላጊ የቅጽል ስም የተሰጠዉ መለስ ዜናዊ በ2004 ዓም ሐምሌ ላይ ከዚህ አለም በሞት ሲለይ ዜናዉ ለኢትዮጵያ ህዝብ የተነገረዉ በነኀሴ ወር ማለቂያ ላይ ነበር እሱም ቢሆን ሞትን ያክል ነገር ደብቆ ማቆየት ስለማይቻል ነዉ እንጂ አይነግሩንም ነበር። ከዚህ በተጨማሪ በሰሜናዊዉ የአገራችን ከፍል ወያኔ ከጎረቤት አገር ጋር የተዋዋለዉ መሬት ቆርሶ የመስጠት ዉል የኢትዮጵያ ህዝብ ሳያዉቀዉና ሳይሰማዉ የተደረገ ዉል ወይም ስምምነት ነዉ።
አርበኞች ግንቦት ሰባት አገራችን ኢትዮጵያ በአባይ ወንዝ ላይ ብቻ ሳይሆን ከግዛቷ ተነስተዉ ወደ ጎረቤት አገሮች በሚፈሱ አለም አቀፍ ወንዞቿና በሌሎችም የአገር ዉስጥ ወንዞቿ ላይ ግደብ የመስራት ማንም ሊጋፋዉ የማይገባ የተፈጥሮ መብት አላት ብሎ ያምናል። በሌላ በኩል ደግሞ አባይን በመሳሰሉ ድንበር ዘለል ወንዞች ላይ የሚሰሩ ምንም አይነት የልማት ፕሮጀክቶች በዛቻና በማንአለብኝነት ሳይሆን በመግባባት፤ በመመካከርና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶችን በሚያዳብሩ መልኩ መሰራት አለባቸዉ ብሎም ያምናል። አርበኞች ግንቦት ሰባት ይህንን የሚለዉ ደግሞ መሠረታዊ ኑሯቸዉ በአባይ ወንዝ ላይ አገሮች ሊያደርሱ የሚችሉትን የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ጫና በመፍራት ሳይሆን ትላልቅ የልማት ፕሮጀክቶች ከመጀመራቸዉ በፊት ፕሮጀክቶቹን አስመልክቶ ሊነሱ የሚችሉ ዋና ዋና ልዩነቶች መወገድ አለባቸዉ፤ ልዩነቶችን ለማስወገድ ደግሞ የተሻለና አዋጭ የሆነዉ አማራጭ ዲፕሎማሲ ነዉ የሚል ጽኑ አምነት ስላለን በቻ ነዉ።
የወያኔ አገዛዝ እንደ ፈረንጆቹ ዘመን አቆጣጠር በ2011 ዓም የህዳሴዉን ግድብ ስራ ሲጀምር ከአራት ነጥብ ስምንት ቢሊዮን ዶላር ወይም 96 ቢሊዮን ብር በላይ የተገመተዉ ግዙፍ ግድብ ስራ ሙሉ በሙሉ ከአገር ዉስጥ የገንዘብ ምንጮች በሚገኝ ገንዘብ እንደሚሰራና አገዛዙ ግድቡንና የግድቡን ስራ አስመልክቶ ምንም አይነት ድርድር ከማንም አገር ጋር እንደማያደርግ ለለህዝብ ቃል ገብቶ ነበር። የግድቡ ስራ በተጀመረ በጥቂት አመታት ዉስጥ የግድቡ ግንባታ የአገሪቱን የካፒታል ጥሪት ሙጢጥ አድርጎ በመብላቱና በሌሎች በተጀመሩና ሊጀመሩ በእቅድ በተያዙ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ በግልጽ የሚታይ አሉታዊ ተፅዕኖ ማድረግ በመጀመሩ አለም ባንክ፤ አለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅትና አያሌ ኢትዮጵያዉያን ምሁራን የግድቡ ስራና ግድቡ ላይ የሚፈሰዉ የካፒታል ብዛት እንደገና እንዲታሰብበት ምክር ለግሰዉ ነበር፤ ሆኖም ምክሩ የተሰጠዉ የሚሰማ ጆሮ ለሌለዉ ለወያኔ ነበርና ሰሚ ታጣ። ዛሬ ግድቡ ከተጀመረና ወያኔም በህዳሴዉ ግድብ ላይ ከምንም ከማንም አልደራደርም ካለ ከአራት አመታት በኋላ አንደኛ የግድቡ ፕሮጀክት ስራ በገንዘብ እጥረት የተነሳ እንዲዘገይ ተደርጓል፤ ሁለተኛ ወያኔ የህዳሴዉን ገድብ አስመልክቶ ከግብፅና ከሱዳን መንግስታት ጋር ስምምነት ላይ ደርሶ የፊታችን መጋቢት 14 ቀን ስምምነቱን ለመፈረም ጎንበስ ቀና እያለ ነዉ።
ለመሆኑ ይህ ወያኔ ከሱዳንና ከግብፅ ጋር የህዳሴዉን ግድብ አስመልክቶ የሚፈራረመዉ የስምምነት ዉሳኔ ይዘት ምንድነዉ? ዉሳኔዉ በሦስቱ አገር መሪዎች ፊርማ ከመፅደቁ በፊት ለምንድነዉ የዉሳኔዉ ባለቤት የሆነዉ የኢትዮጳያ ህዝብ እንዲያዉቀዉ ያልተደረገዉ? ባለፉት አራት አመታት ኢትዮጵያ ዉስጥ ምንም አይነት ገቢ ከሌላቸዉ ከተማሪዎችና ከአረጋዉያን ጀምሮ እስከ ቀን ሰራተኛዉ ድረስ ለህዳሴዉ ግድብ ግንባታ ገንዘብ አዋጣ ወይም ቦንድ ግዛ እየተባለ በሩ ያልተንኳኳ ኢትዮጵያዊ የለም። ታዲያ ይህ የኢትዮጵያ ህዝብ በራሱ ገንዘብ ለዕድገቴና ለብልፅግናዬ መሠረት ይሆነኛል ብሎ የሚያሰራዉ ግድብ ስራዉ በገንዘብ እጥረት ሲተጓጎልና በዚሁ ግድብ ዙሪያ ከዉጭ መንግስታት ጋር አለም አቀፍ ስምምነቶች ሲደረጉ ምንም የማይነገረዉ ለምንድነዉ?
የወያኔ መሪዎች ከሱዳንና ከግብጽ መሪዎች ጋር የህዳሴዉን ግድብ አስመልክቶ የተዋዋሉትን ዉል እንመራዋለን ብለዉ ከሚናገሩት ህዝብ ቢደብቁም ካርቱምና ካይሮ ወስጥ ሾልከዉ የወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ግብፅ የህዳሴዉ ግደብ ፕሮጀክት ላይ የቁጥጥርና የማነጅመንት ድርሻ አንደሚኖራት እየተነገረ ነዉ። እንደዚህ አይነቶቹ ከዚህ ቀደም በፍጹም የማይሞከሩ ወይም የማይታሰቡ ናቸዉ ተብለዉ ሲነገሩ የነበሩ ስምምነቶችና ዉሎች ዛሬ ተደርገዉና የሶስትዮሽ ስምምነት ተደርሶባቸዉ በፊርማ የሚጸድቁት ግድቡን ሰርቶ ለመጨረስ የሚያስፈልግ ገንዘብ ለማግኘት ነዉ ወይስ ሌላ ድብቅ አላማ አለዉ? ደግሞስ ግድቡ የሚሰራዉ ለህዝብ ግድቡን የሚሰራዉም ህዝብ ሆኖ ሳለ ለምንድነዉ ይህ በዉድም በግድም ገንዘብ ካላዋጣህ ወይም ቦንድ ካልገዛህ እየተባለ ቀንና ማታ ሲጠየቅ የኖረ ህዝብ በዚህ ግድብ ዙሪያ የሚደረጉ ዉሎችንና ስምምነቶችን እንዳያዉቅና ጭራሽ እንዳይሰማ የተደረገዉ? ካይሮና ካርቱም ዉስጥ እንደሚነገረዉ ግብፅ በህዳሴዉ ግድብ ግንባታ ዙሪያ የማነጅመንትና የቁጥጥር ሚና ይኖራታል የተባለዉ ዜና እዉነት ከሆነ እኛ እራሳችን አገራችን ዉስጥ በምንሰራዉ ግድብ ግብፅ ሊኖራት የሚችለዉ የማነጅመንትና ቁጥጥር ድርሻ ዬት ድረስ ነዉ የሚሆነዉ …ለምንስ እንዲህ አይነት ሚና እንዲኖራት ተደረገ?
አርበኞች ግንቦት ሰባት የሶስቱ አገሮ መሪዎች ስምምነቱን በፊርማ ከማጽደቃቸዉ በፊት የኢትዮጵያ ህዝብ ለእንደነዚህ አይነት ቁለፍ ጥያቄዎች መልስ ማግኘት አለበት ብሎ ያምናል። የኢትዮጵያ ህዝብ ኢትዮጵያን አስመልከቶ የሚደረጉ ምንም አይነት ዉሎችና ስምምነቶች ብቸኛዉ ባለቤት ነዉና ከዚህ ህዝብ ተደብቆ የሚደርግ ምንም አይነት ስምምነት ሊኖር አይገባም። ስለዚህም የኢትዮጵያ ህዝብ እነዚህ ከዚህ በላይ ያነሳናቸዉ ጥያቄዎች ጥርት ባለ መልኩ እንዲመለሱለት የወያኔን አገዛዝ ማስጨነቅ አለበት፤ አለዚያ ይህ ጉዳይ ዉሎ ካደረ በኋላ የሚደረገዉ ሩጫ ሁሉ “ቁጭ ብለዉ የሰቀሉትን ቆሞ ማዉረድ ያቅታል” እንደሚባለዉ ይሆናል።
ግብፅና ሱዳን የረጂም አመታት ወዳጅነትና አመታት ያስቆጠረ ወተዳራዊ ስምምነት ያላቸዉ ተጎራባች አገሮች ናቸዉ። እነዚህ ሁለት አገሮች በቅርቡ ከወያኔ ጋር የደረሱበትን ስምምነት “የግብፅን ፍላጎት የሚያረካ” ስምምነት ነዉ እያሉ ካርቱምና ካይሮ ዉስጥ አስተያየት በመስጠት ላይ ሲሆኑ ኢትዮጵያ ዉስጥ ግን ሁሉም ነገር ህዝብ እንዳያዉቀዉ በሚስጢር መያዙ እየታወቀ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት “አዲስ ምዕራፍ” ተከፈተ እያለ የፈረደበትን የኢትዮጵያ ህዝብ መሸንገል ጀምሯል። በሌላ በኩል ደግሞ ወያኔ ሱዳንና ግብፅ በቅርቡ ካርቱም ላይ የደረሱበት ስምምነት እዚያዉ ካርቱም ዉስጥ የፊታችን ሰኞ በሦስቱ አገሮች መሪዎች ፊርማ ይጸድቃል ተብሎ በሚጠበቅበት በአሁኑ ወቅት የግብጹ ፕሬዚዳንት አብዱል ፈታ አል ሲሲ የዉጭ ጉዳይና የዉኃ ኃብት ልማት ሚኒስተራቸዉን አስጠርተዉ ሦስቱ አገሮች የደረሱበትን ሰነድ መርምረዉ ሪፖርት እንዲያቀርቡላቸዉ ማዘዛቸዉ ከወደ ካይሮ ተደምጧል። እንግዲህ ይታያችሁ እኛ ኢትዮጵያዉያን የሦስቱ አገሮች ስምምነት ምን እንደሆነ እንኳን ሳናዉቅ ግብፅ እሷ እራሷ የደረሰችበት ስምምነት አልጥም ብሏት ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጣት ጠይቃለች። ይህ የሚያሳየን አገሮች ለብሄራዊ ጥቅማቸዉና ደህንነታቸዉ ምን ያህል እንደሚጨነቁና አርቀዉ የሚመለከቱ አስተዋይ መሪዎች ደግሞ የሚጨንቃቸዉና የሚያሳስባቸዉ ይህ አሁን የሚመሩት ህዝብ ብቻ ሳይሆን ወደፊት በተከታታይ የሚመጣዉ ትዉልድ ጭምር መሆኑን ነዉ።እኛ ኢትዮጵያዉያን ግን ለእንደዚህ አይነት መሪዎች አልታደልንም። የኛ መሪዎች እንኳን ለሚመጣዉ ትዉልድ ሊጨነቁ ለዛሬዉም ትዉልድ “እኛ ከሞትን ሠርዶ አይበቀል” የሚሉ ስግብግቦች ናቸዉ።
ወያኔ ከራሱ ዉጭ ማንንም የማይሰማ፤ልዩነትን የማያስተናግድና የሌሎችን ሃሳብ ከሱ ሀሳብ የተሻለ መሆኑን እያወቀም ቢሆን የማይቀበል ችኮ መሆኑን በተደጋጋሚ አሳይቶናል። ዛሬ ላይ ቆመን ወደ ኋላ ዞር ብለን የትናንቱን ስንመለከት ወያኔ በህዳሴዉ ግድብ ዙሪያም ገና ከጥንስሱ ጀምሮ ያሳየን ይህንኑ ችኮነቱንና “እኔን ብቻ ስሙ” ባይነት ዕብሪቱን ነዉ። በተለይ የህዳሴዉን ግደብ በተመለከተ አባይ ወንዝ ላይ የሚገነባዉ ግድብ ከዚህ ቀደም በማንም ኢትዮጵያዊ ያልታሰበና የልተወጠነ ፍጹም አዲስ የሆነ ወያኔ ለኢትዮጵያ ያበረከተዉ ገጸ በረከት መሆኑን ለማሳየት ብዙ ጥሯል፤ አንዳንድ የዋሆችን ደግሞ አሳምኗል።ወያኔ ሁሌም ቢሆን ጥረቱና ፍላጎቱ እራሱን ከብጤዉ ከደርግ ጋር እያወዳደረ የተሻለ ሆኖ ለመታየት መሞከር ነዉ እንጂ የተሻለ ስራ መስራት ስላልሆነ በህዳሴዉ ግድብ ላይም አብዛኛዉን ግዜ ያጠፋዉ “አባይን የደፈረ” ተብሎ ለመጠራት ስለሆነ ዛሬ ግድቡ ግንባታዉ አልቆ አገልግሎት መስጠት በሚጀምርበት ወቅት የግድቡ ስራ ከመጀመሩ በፊት ተሰርተዉ ማለቅ የነበረባቸዉን ስራዎች እየሰራ ነዉ።
በቅርቡ አንድ አለም አቀፍ የጋዜጠኞች ቡድን ግድቡ የሚሰረባት ቦታ ድረስ በመሄድ የፕሮጀክቱን እንቅስቃሴ በተመለከተ ጥናት አትንቶ የግድቡ ስራ በከፍተኛ የገንዘብ እጥረት የተነሳ ይዘገያል ብሎ ሪፖርት ማቅረቡ የሚታወስ ነዉ። ጉዳዩን በቅርብ ለምናዉቀዉ ለኛ ለኢትዮጵያዉያን ግን እዉነቱ ከዚህ በላይ ነዉ። የህዳሴዉ ግደብ የሚዘገየዉ በገንዘብ እጥረት ብቻ አይደለም። የዚህ ትልቅ ፕሮጀክት ድህረ ጥናት ሁኔታዎችን የላጤነና ቅደም ተከተሎችን ያላገናዘበ ጎደሎ ጥናት ነበር፤ ከዚህ በተጨማሪ ሩጫዉና ግርግሩ የተጀመረዉ የህዳሴዉን ግደብ የመሰለ ግዙፍ የ96 ቢሊዮን ብር ፕሮጀክት በይድረስ ይድረስ ሰርቶ ለመጨረስ ነበር።
የብዙ አለም አቀፍና የአገር ዉስጥ ኤክስፐርቶች ግምት በግልጽ እንደሚጠቀመዉ የህዳሴዉን ገድብ ግንባታ ጨርሶ አግልግሎት የሚሰጥበት ደረጃ ላይ ለማድረስ ፕሮጀክቱ በዕቅድ ከተያዘለት በጀት ከሃምሳ በመቶ በላይ ሊያስፈልገዉ ይችላል። ይህ ደግሞ ዛሬ ወያኔን ስለምንቃወም የምናወራዉ ተራ የፕሮፓጋናዳ ጨዋታ ሳይሆን የዛሬ አራት አመት ወያኔ ከበቂ ጥናትና ዝግጅት ዉጭ አባይን እገድባለሁ ብሎ ሲፎክር የዛሬዋ ቀን እንደምትመጣ አዉቀን በተከታታይ ያስጠነቀቅነዉ ማስጠንቀቂያ ስለሆነ ነዉ። ይህ ሁሉ የሚያሳየን ወያኔ አስቀያሚ መልኩን ለማሳመር ሲል ብቻ በኢትዮጵያ ህዝብ ገንዝብና ጉልበት የህፃን ጨዋታ መጫወቱን ነዉ። ሆኖም ዛሬ የሚያስፈራን ይህ ወያኔ የተጫወተበት መጠነ ብዙ የህዝብ ገንዘብ ብቻ ሳይሆን ግድቡን ሰርቶ ለመጨረስ ተጨማሪ ገንዘብ ለማግኘት የሚያደርገዉ አጉል መቅበዝበዝ ነዉ። በእኛ እምነት የህዳሴዉ ግደብ ተሰርቶ ሲያልቅ ኢትዮጵያን ከጥገኝነት ነፃ ማዉጣት ነዉ ያለበት እንጂ ሌላ አላስፈላጊ የሆነ የፖለቲካ ጥገኝነት ዉስጥ ይዞን መግባት የለበትም። ለዚህም ነዉ አርበኞች ግንቦት ሰባት ወያኔ፤ ግብፅና ሱዳን በአባይ ወንዛችን ላይ የሚሰራዉን ግድብ አስመልክቶ ደረስን የሚሉትን ስምምነት ምኑም ሳይደበቅ ለኢትዮጵያ ህዝብ በግልጽ መነገር አለበት እያለ ህዝብንም ወያኔንም የሚያስጠነቅቀዉ። የግብፅና የሱዳን መንግሰታት አገራቸዉ ዉስጥ ህዝብ የሚወዳቸዉ ወይም የሚጠላቸዉ መንግስታት ሊሆኑ ይችላሉ፤ ሆኖም ከዉጭ መንግሰታት ጋር በሚያደርጉት ምንም አይነት ድርድርና ዉይይት ሽንጣቸዉን ገትረዉ የሚቆሙት ለአገራቸዉ ጥቅም ብቻ ነዉ እንጂ ሌላ ከህዝብና ከአገር የተለየ አጀንዳ የላቸዉም። ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ አገዛዝ በተለይ ባለፉት ሃያ አራት አመታት ብቻዉን ስልጣን ተቆጣጥሮ የኖረዉ ህወሓት ግን ከኢትዮጵያ ህዝብ ዘለቄታዊ ጥቅም የተለየ የራሱ የሆነ አጀንዳ አለዉ። አርበኞች ግንባት 7 ህወሓትንና ይህንን ከህዝብና ከአገር የተለየ አጀንዳዉን የማቆሚያዉ ግዜ ዛሬ ነዉና ጉልበት ያለህ በጉልበትህ፤ ገንዘብ ያለህ በገንዘብህ፤ እዉቀት ያለህ ደገሞ በእዉቀትህ ነገ ሳይሆን ዛሬ ህዝባዊዉን ትግል ተቀላቀል እያለ አገራዊ ጥሪ ያስተላልፋል።

‘Declaration of Principles’ signed by Egypt, Sudan and Ethiopia

In an important step towards resolving a long-running dispute over the Grand Renaissance Dam, the leaders of Egypt, Ethiopia and Sudan have signed in Khartoum a declaration of principles as follows
File photo: A general vGrand Renaissance dam in Guba Woreda, Benishangul Gumuz region
File photo: A general view shows construction activity on the Grand Renaissance dam in Guba Woreda, Benishangul Gumuz region March 16, 2014 (Photo: Reuters)
Ahram Online publishes a translated version of the “Declaration of Principles” signed by Egypt, Sudan and Ethiopia in a step to put an end to a four-year dispute over Nile water sharing arrangements among Nile Basin countries. Ten principles are outlined in the document signed by the three countries.
Introduction
Valuing the increasing need of the Arab Republic of Egypt, the Federal Democratic Republic of Ethiopia and the Republic of the Sudan for their over-border water sources, and realising the importance of the Nile River as a source of life and a vital source for the development of the people of Egypt, Ethiopia and Sudan, the three countries have committed themselves to the following principles concerning the Grand Ethiopian Renaissance Dam:
1. Principle of cooperation:
– Cooperation based on mutual understanding, common interest, good intentions, benefits for all, and the principles of international law.
– Cooperation in understanding the water needs of upstream and downstream countries across all their lands.
2. Principle of development, regional integration and sustainability:
– The purpose of the Renaissance Dam is to generate power, contribute to economic development, promote cooperation beyond borders, and regional integration through generating clean sustainable energy that can be relied on.
3. Principle of not causing significant damage:
– The three countries will take all the necessary procedures to avoid causing significant damage while using the Blue Nile (the Nile’s main river).
– In spite of that, in case significant damage is caused to one of these countries, the country causing the damage […], in the absence of an agreement over that [damaging] action, [is to take] all the necessary procedures to alleviate this damage, and discuss compensation whenever convenient.
4. Principle of fair and appropriate use:
– The three countries will use their common water sources in their provinces in a fair and appropriate manner.
– To ensure fair and appropriate use, the three countries will take into consideration all guiding elements mentioned below:
a. The geographic, the geographic aquatic, the aquatic, the climatical, environmental elements, and the rest of all natural elements.
b. Social and economic needs for the concerned Nile Basin countries.
c. The residents who depend on water sources in each of the Nile Basin countries.
d. The effects of using or the uses of water sources in one of the Nile Basin countries on another Nile Basin country.
e. The current and possible uses of water sources.
f. Elements of preserving, protecting, [and] developing [water sources] and the economics of water sources, and the cost of the procedures taken in this regard.
g. The extent of the availability of alternatives with a comparable value for a planned or a specific use.
h. The extent of contribution from each of the Nile Basin countries in the Nile River system.
i. The extent of the percentage of the Nile Basin’s space within the territories of each Nile Basin country.
5. The principle of the dam’s storage reservoir first filling, and dam operation policies:
– To apply the recommendations of the international technical experts committee and the results of the final report of the Tripartite National Technical Committee during different stages of the dam project.
– The three countries should cooperate to use the final findings in the studies recommended by the Tripartite National Technical Committee and international technical experts in order to reach:
a. An agreement on the guidelines for different scenarios of the first filling of the Grand Ethiopian Renaissance Dam reservoir in parallel with the construction of the dam.
b. An agreement on the guidelines and annual operation policies of the Renaissance Dam, which the owners can adjust from time to time.
c. To inform downstream countries, Egypt and Sudan, on any urgent circumstances that would call for a change in the operations of the dam, in order to ensure coordination with downstream countries’ water reservoirs.
– Accordingly the three countries are to establish a proper mechanism through their ministries of water and irrigation.
– The timeframe for such points mentioned above is 15 months from the start of preparing two studies about the dam by the international technical committee.
6. The principle of building trust:
– Downstream countries will be given priority to purchase energy generated by the Grand Ethiopian Renaissance Dam.
7. The principle of exchange of information and data:
– Egypt, Ethiopia and Sudan will provide the information and data required to conduct the studies of the national experts committees from the three countries in the proper time.
8. The principle of dam security:
– The three countries appreciate all efforts made by Ethiopia up until now to implement the recommendations of the international experts committee regarding the safety of the dam.
– Ethiopia will continue in good will to implement all recommendations related to the dam’s security in the reports of the international technical experts.
9. The principle of the sovereignty, unity and territorial integrity of the State:
The three countries cooperate on the basis of equal sovereignty, unity and territorial integrity of the state, mutual benefit and good will, in order to reach the better use and protection of the River Nile.
10. The principle of the peaceful settlement of disputes:
The three countries commit to settle any dispute resulting from the interpretation or application of the declaration of principles through talks or negotiations based on the good will principle. If the parties involved do not succeed in solving the dispute through talks or negotiations, they can ask for mediation or refer the matter to their heads of states or prime ministers.

272 days and counting for Andargachew Tsege on death row

In June 2014, political activist Andargachew Tsege was captured in Yemen and sent to a secret prison in Ethiopia.

by Keila Guimaraes | Lslington Now
The wife of a British national on death row has been fighting a long legal battle to free her husband after he was rendered by Ethiopian forces last year.Andargachew Tsege on death row
Islington resident Yemi Hailemariam has been petitioning Downing Street in order to put pressure on the Foreign Commonwealth Office, but says she has seen little improvement.
The political activist Andargachew Tsege was flying from Yemen to Dubai on 23 June 2014 when he was captured in a Yemenese airport and sent to Ethiopia against his will. His family found out his whereabouts a week later when the Yemen government confirmed the operation.
Hailemariam said:
When I knew the truth, it was heart-breaking to say the least. It was the day that changed our lives.
Tsege has a long history of animosity with Ethiopian politicians. He flew out of the country in 1979 at the age of 24 as a political refugee and found shelter in England, where he gained British citizenship status. He settled in Islington, but continued campaigning and visiting Ethiopia.
He joined the movement GINBOT 7, which was formed in 2008 by politicians and activists in exile. The party, whose agenda is to overthrow the ruling party, was labelled as a terrorist group by Ethiopia in 2011. Tsege has been charged with terrorism and sentenced to death in absentia twice, in 2009 and 2012.

The legal battle

Since her husband’s imprisonment, Hailemariam has started a legal battle to free Tsege. Her campaign eventually gained the attention of Prime Minister David Cameron, who wrote to the Ethiopian Prime Minister Hailemariam Desalegn last October asking for consular access to Tsege and for the death penalty not to be imposed. Tsege was granted only two visits with the British ambassador, on 11 August 2014 and 19 December 2014, but has had no access to lawyers.
Ethiopia has also vetoed a visit from Tsege’s MP, Jeremy Corbyn, who was scheduled to travel to the country on 13 February.
Hailemariam argues that the Ethiopian government has breached international law. She says:
It was an illegal procedure. Citizens have legal rights; they can’t be removed from a country against their will without informing their embassy. That’s kidnapping.
In its 2015 report, advocacy group Human Rights Watch called attention to Tsege’s case: “The transfer violated international law prohibitions against sending someone to a country where they are likely to face torture or other mistreatment.”
A Foreign Commonwealth Office (FCO) spokesperson has also declared that Tsege’s rights have not been respected. “We remain deeply concerned that Andargachew Tsege is being detained in Ethiopia without being granted his rights to regular consular visits or access to a lawyer. We have repeatedly raised this with the Ethiopian authorities and will continue to do so.”

70,000 strong petition

In February, Hailemariam handed a petition with more than 70,000 signatures to Downing Street to ask the British government to put pressure on Ethiopia. But she said that she is in the battlefield alone and that the FCO has been too lenient.
“The FCO is driven by pressure, not by principles. And it infuriates me.”
But lenience might not be the only element in this diplomatic puzzle.
Ethiopia is an important economic partner for the UK and a strong ally on counter-terrorism activities in the region. In the next two years, the UK is investing £303 million in the country.
“Ethiopia lies at the heart of an unstable region that has experienced almost continuous conflict and environmental shocks in recent decades”, detailed the Department for International Development (DFID) in a document about investment in Ethiopia.
It concluded that “a stable, secure and prosperous Ethiopia is critical to UK interests”.

“Ethiopian security forces are responsible for the kidnap, torture and death sentence of British national Andargachew Tsege”

For legal charity Reprieve, the British government is putting economic and security reasons above international law.
Maya Foa, director of Reprieve’s death penalty team, said:
Ethiopian security forces are responsible for the kidnap, torture and death sentence of British national, Andargachew Tsege. Instead of dodging questions and then secretly shelving embarrassing programmes, DFID [Department for International Development] should be explaining why it was using taxpayers’ money to fund these forces in the first place – and what safeguards, if any, it put in place to ensure this ‘high risk’ funding did not enable abuses of the kind suffered by Mr Tsege.
Despite the complexity of Tsege’s case, Hailemariam says she has not given up hope.
“The only thing I see is that we cannot stop. I believe something will work out because we live in a society where I understand civil rights matter. That is very important. Even if the government doesn’t believe so, society believes this kind of thing is unacceptable. I believe we can make progress.”
The movement “Free Andargachew” is organising a protest in front of the FCO office this Friday to demand his immediate release. On Friday, Tsege will have spent 276 days in prison.

Wednesday, March 18, 2015

“ስሉሱ” ዞረ እንዴ?!

የምዕራቡ ሚዲያና ኢህአዴግ
eprdf and western media
ከጥቂት ሳምንታት ወዲህ ባልተለመደ ሁኔታ ኢህአዴግ ላይ ታዋቂ የዓለማችን ጋዜጦች የጀመሩት ተከታታይ ትችት፣ ማሳሰቢያና መፍትሔ ጠቋሚ ዘገባዎች መነጋገሪያ አጀንዳ ሆነዋል፡፡ ሚዲያዎቹ በዘገባቸው ኢህአዴግን ከቻይና አምባገነናዊና አክራሪ አገዛዝ ጋር አመሳስለዋል፡፡ ኢህአዴግ እከተለዋለሁ የሚለውን የኢኮኖሚ መርህ ከቻይና የተኮረጀ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ውጤቱም ሆነ መድረሻው ግራ የሚያጋባና የማይታወቅ እንደሆነ ዘግበዋል፡፡ ጋዜጦቹ ኢህአዴግን በሚንከባከቡት መንግሥቶቻቸው እና በራሱ ኢህአዴግ ላይ የሰላ ሒስ መሰዘንዘር መጀመራቸው የፖሊሲ አውጭዎችን አስተሳሰብ የሚያስቀይር ከመሆን አልፎ ኢህአዴግ ላይ “ስሉሱ” ዞሯል የሚያስብል እንደሆነም ተጠቁሟል፡፡
ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም” በሚል ርዕስ የሰብዓዊ መብት ተመልካች የሆነው ድርጅት (ሂዩማን ራይትስ ዎች) ኢህአዴግ በሚያደርስባቸው ስልታዊ አፈና፣ ማስፈራሪያ፣ ህይወት የማጥፋት ዛቻ፣ … ምክንያት ኢትዮጵያ በጋዜጠኞች ላይ አፈና በማድረግ የቀዳሚነቱን ስፍራ መያዟን ባለ 76 ገጽ ዘገባ ካወጣ በኋላ በምዕራቡ ዓለም ያሉ ሚዲያዎች በኢህአዴግ አፋኝነት ላይ ጠንከር ያሉ ዘገባዎችን ማውጣታቸውን ይፋ እየሆነ መጥቷል፡፡
በዚህ ረገድ ቀዳሚውን ቦታ የወሰደው በዋሽንግቶን ዲሲ የአሜሪካ ፖሊሲና ሕግ አውጪዎችን አቅጣጫ በማመላከት የሚታወቀው “ዋሽንግቶን ፖስት” የዛሬ ወር አካባቢ የሰብዓዊ መብት ድርጅቱን ዘገባ ተተርሶ (የታፈነው የኢትዮጵያ ፕሬስ) “Ethiopia’s stifled press” በሚል ርዕስ አቋም የያዘበት ርዕሰ አንቀጽ ነው፡፡ ጋዜጣው እንዳለው በሟቹ መለስ የተጀመረው አፈና በቀጣዩ ሃይለማርያም አገዛዝም በይበልጥ እየከረረ መሄዱን ጠቁሟል፡፡ በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያ ከባላንጣዋ ኤርትራ እየባሰች መምጣቷን እንዲያው በተሻለ ሁኔታ ኤርትራ በጥር ወር ውስጥ በርካታ ጋዜጠኞችን ከእስር መፍታቷን ጨምሮ ገልጾዋል፡፡ ጋዜጣው ግልጽና የጠነከረ አቋም በወሰደበት በዚህ ርዕሰ አንቀጽ ማብቂያ ላይ አሜሪካ ለኢህአዴግ ዋንኛ ድጋፍ ሰጪ መሆኗን በመናገር በ2014 ለልማት ዕርዳታ በሚል 373 ሚሊዮን ዶላር መስጠቷን አስረድቷል፡፡ በአንጻሩ አሜሪካ ለዴሞክራሲና ለሰብዓዊ መብት ጥበቃ ማስፋፊያ ለኢትዮጵያ የምትሰጠው ዕርዳታ በ2012ዓም 3.4ሚሊዮን ዶላር የነበረው በ2014ዓም ወደ 163ሺህ ዶላር ማሽቆልቆሉን ተናግሯል፡፡ ይህ የሆነበት ዋንኛ ምክንያት ኢህአዴግ ያወጣው የመያዶች ሕግ እንደሆነ ጋዜጣው ጨምሮ ገልጾዋል፡፡
ዋሽንግቶን ፖስት ርዕሰ አንቀጹን ሲጠቃልል ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ዕርዳታ በማግኘት ቀዳሚ እንደመሆኗ በዴሞክራሲ ዕድገት እየሄደችበት ያለው ጎዳና አጠያያቂ እንደሆነ እንደምታ ያለው ሃሳብ ከሰነዘረ በኋላ የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር መ/ቤት (ስቴት ዲፓርትመንት) እና የኦባማ አስተዳደር እንዲሁም ባጠቃላይ ምዕራባውያን ማድረግ የሚገባቸውን በግልጽ አስቀምጧል፡፡ ስቴት ዲፓርትመንት በኢትዮጵያ እየተደረገ ባለው የሚዲያ አፈና ላይ ተቃውሞውን ማሰማት አለበት፤ ይህም ግን ከቃላት ማለፍ አለበት፤ የኦባማ አስተዳደር የሚሰጠውን ዕርዳታ ጋዜጠኞችና ጦማሪዎች እንዲፈቱ ከመጠየቅ ጋር ማቆራኘት አለበት (የማይፈቱ ከሆነ ዕርዳታ እስከመከልከል)፤ ሌሎች ምዕራባዊ ለጋስ አገራትም ተመሳሳይ እርምጃ እንዲወስዱ ማድረግ አለበት፤ ምዕራባዊ አገራት በአጠቃላይ ጋዜጠኞችን በማሰር በዓለም ታዋቂ ለሆነ አገዛዝ የሚያደርጉትን ዕገዛ ማቆም አለባቸው የሚል በዓይነቱ ተጠቃሽ የሆነና የምዕራቡ ዓለም በኢትዮጵያ ላይ የፖሊሲ ለውጥ እንዲያደርግ ግፊት የሚያደርግ ርዕሰ አንቀጽ ነበር፡፡
anuak woman aboboበቀጣይ የእንግሊዙ “ዘ ጋርዲያን” ኢህአዴግ በምዕራባውያን ዕርዳታ ከዓለም ባንክ የሚያገኘው 98ቢሊዮን ብር እንደነጠፈበት በመዘገብ “በመብት ረገጣ ምክንያት ብሪታኒያ ለኢትዮጵያ ከምትሰጠው ዕርዳታ አፈገፈገች” (British support for Ethiopia scheme withdrawn amid abuse allegations) በሚል ርዕስ ያወጣው ነው፡፡ ኢህአዴግን ከማንገስ ጀምራ በሥልጣን እንዲቆይ እንዲሁም በርካታ ድጋፍ ስትሰጥ የቆየችው እንግሊዝ እንዲህ ዓይነቱን እርምጃ ለመውሰድ መቻሏን ጋዜጣው በሰበር ዜና መልክ ማተሙ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ነው፡፡ ከተወሰኑ ጊዜያት በስተቀር በኢህአዴግ አገዛዝ ላይ የሰላ ሒስ ከመሰንዘር ከሚቆጠቡት የእንግሊዝ ሚዲያዎች አንጻር ዘጋርዲያን የወሰደው አቋም ለየት ያለ ነው፡፡ የእንግሊዙ የልማት ተራድዖ መ/ቤት “ኢትዮጵያ አድጋለች” በማለት ዕርዳታውን ከማቆም በማይተናነስ መልኩ ወደ 5በመቶ ማውረዱን ጋዜጣው ቢጠቅስም “ለዕድገቷ ማስረጃ” እንዲሆን ዜናውን ሲያትም በገዢነት ያወጣው የፎቶ ምስል በድንግዝግዝ ጸሃይ በአቧራ የተሰራ ቤት አቅራቢያ አቧራ ሲጠርጉ የሚታዩ ደካማ የአኙዋክ ሴትን ነው፡፡ የእርዳታው ገንዘብ ይሰጥ የነበረው መሠረታዊ አገልግሎቶችን ማለትም ትምህርት፣ ጤና፣ ንጹህ ውሃ አቅርቦት፣ መንገድ ሥራ፣ ወዘተ ለመሳሰሉ የዜጎችን ኑሮ ለሚያሻሽሉ አስፈላጊ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያነት ነበር፡፡
ያለፈው ሳምንት አጋማሽ ኒው ዮርክ ታይምስ “በድህነት ተዳክማ የነበረችው ኢትዮጵያ በኢኮኖሚ ፍንዳታ እየጋለበች ነው” (Ethiopia, Long Mired in Poverty, Rides an Economic Boom) በሚል ርዕስ በርካታ ጉዳዮችን በመዳሰስ ያወጣው የዜና ዘገባ ሌላው ተጠቃሽ ነው፡፡ ለኢኮኖሚ ዕድገቱ አብነት እንዲሆኑ የዘመኑን ሰዎች እና ባለሃብቶች ጋዜጣው ቃለመጠይቅ በማድረግ በቂ ሽፋን ሰጥቷል፡፡ በአዲስ አበባ ውስጥ ጎልተው የሚታዩ እና “ከዕድገቱ” ጋር በንጽጽር ሊቀርቡ የሚገባቸውን ጉዳዮችንም ዳስሷል፡፡ በከተማዋ የተንሰራፋው ድህነት፣ የመገናኛ ዕጥረት፣ የኤሌክትሪክ መቋረጥ፣ የኢንተርኔት ኤሊነት፣ የቴሌኮሙኒኬሸን ኢተዓማኒነት፣ ወዘተ ላይ ጋዜጣው የሰላ ሒስ ሳያነሳ አላለፈም፡፡ ኢህአዴግ የሚታመንበትን የዓለም ባንክ ኃላፊንም አነጋግሯል፡፡ በኢትዮጵያ የባንኩ ዳይሬክተር የሆኑት ጉዋንግ ቼን አሁን አጠቃላይ ያለው አሠራር ተጠቃሽ መሆኑ ከገለጹ በኋላ ሲቀጥሉ “እንዲህ ያለው የኢኮኖሚ ሞዴል ለኢትዮጵያ ሰርቷል፤ ጥያቄው ቀጣይነት አለው? የሚለው ነው፤ ባንኩም ይህንኑ በመጠየቅ የኢኮኖሚው ሞዴል ለሚቀጥሉት 10 ዓመታት መቀጠል ይችላል ወይ? በማለት ይጠይቃል፤ በእኛ አመለካከት መልሱ አይችልም ነው” ማለታቸውን ጋዜጣው ጨምሮ ዘግቧል፡፡
ለማመዛዘን የተቃዋሚዎችን ሃሳብ ያቀረበው ጋዜጣ በፖለቲካው ረገድ ቀልብ የሚስቡ ሃሳቦችን አስፍሯል፡፡ ተቺዎች ያሉት ነው በማለት የመንግሥት አስተዳደር በትግሬዎች የበላይነት ቁጥጥር ሥር መውደቁን፣ ህወሃት ምንም ዓይነት ተቃውሞ መስማት የተሳነው መሆኑን፣ የተቃዋሚው እንቅስቃሴ (በትግሬዎች) የቁጥጥር መረብ ውስጥ የወደቀ መሆኑን፤ ፓርላማው በኢህአዴግ የበላይነት “የሚነዳ” መሆኑን፤ ማንኛውም የተቃውሞ ድምጽ የታፈነ መሆኑን፤ ጋዜጣው ማስረጃዎችን በማጣቀስ ሃተታውን ሰጥቷል፡፡ ሲያጠቃልልም የዞን 9 ጠበቃ የሆኑትን አቶ አመሃ መኮንን የሰጡትን አስተያየት ጠቅሷል፡፡ “በመንግሥትና በሕዝብ መካከል መተማመን መኖሩ ለዕድገት ጠቃሚ ነው፤ ነገር ግን እንዲህ ዓይነቱ መተማመን አለ ብዬ ለማመን አልችልም” በማለት የሕግ ባለሙያው ተናግረዋል፡፡
ከጥቂት ቀናት በፊት ደግሞ “ዎል ስትሪት ጆርናል” ኢህአዴግ የሚከተለው የልማት ፕሮግራም የተቃዋሚውን ድምጽ እንዲታፈን ያደረገ መሆኑን በመጥቀስ “Ethiopia’s Growth Program Cuts Out Dissent” በሚል ርዕስ  ዘገባ አስነብቧል፡፡ በኢህአዴግ ፓርላማ ፓርቲ አልባ ብቸኛ “የተቃዋሚ ፓርቲ አባል” በሆኑትን አቶ ግርማ ሰይፉ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ “ገዢው ፓርቲ ምርጫውን ያጠናቀቀው” መሆኑን በመግለጽ መጪው ምርጫ አስቀድሞ የተወሰነ መሆኑን ዘግቧል፡፡ በቻይና ስልት ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው ኢህአዴግ ተቃዋሚዎቹን ሁሉ በሚፈልገው መልኩ ጸጥ ያሰኘ መሆኑን ያተተው ጋዜጣ ስልቱን ሲተነትን የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ከጋዜጠኛ ጋር በፖለቲካ ጉዳዮች ለመነጋገር እንደሚፈሩ፤ የስልክ ጥሪዎች ክትትል እንደሚደረግባቸው፤ አገዛዙን የሚተቹ ድረገጾች ውታፍ የተደረገባቸው እንደሆነ፤ የኢህአዴግን አገዛዝ የሚተች ማንኛውም ሰው ሥራ ለማግኘት፣ ንግድ ለማከናወን፣ ጨረታ ለማሸነፍ፣ ወዘተ የሚቸገር መሆኑን፤ ከነዋሪዎች ቃርሞ ባገኘው መረጃ አስረድቷል፡፡girma seifu maru
ከኢህአዴግ ሹሞች ስለታሰሩት ጋዜጠኞች ጉዳይ የአጸፋ ምላሽ ያሰፈረው ዎል ስትሪት አፈቀላጤው ሽመልስ ከማል የታሰሩት “ጋዜጠኞች አለመሆናቸውን” የታሰሩትም ሃሳባቸውን በመግለጻቸው አለመሆኑን ጋዜጣው ለንጽጽር አቅርቧል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘየሰብዓዊ መብት ተመልካቹ መ/ቤት በሚዲያ እና ጋዜጠኞች ላይ ያወጣውን ዘገባ በማጣቀስ በኢትዮጵያ የሚካሄደውን የሰብዓዊ መብት ረገጣና በጋዜጠኞች ላይ የሚፈጸመውን እንግልት ለአብነት አስፍሯል፡፡ በመልካም አስተዳደር እና በሌሎች ጉዳዮች አገሪቱ ወደታች እያሽቆለቆለች እንደሆነ የተናገረው ዎል ስትሪት ጆርናል በቅርቡ በተካሄዱ ሰላማዊ ሰልፎች የአገዛዙ ጥበቃ ኃይላት በሰልፈኞች ላይ ጥይቶች መተኮሳቸውን ዘግቧል፡፡
መጪው ምርጫ ብዙም ተስፋ የሚጣልበት እንዳልሆነ በሃተታው እንደምታ የገለጸው ጋዜጣ የምዕራባውያንን ዝምታ ሳይጠቅስ አላለፈም፡፡ አሜሪካ ከኢህአዴግ ጋር ባላት የአካባቢው ጸጥታና የሰላም ጥበቃ ውል ምክንያት የራሷን ጥቅም የምታይ ብቻ መሆኗን ጋዜጣው ያስረዳል፡፡ በመሆኑም አቶ ግርማ እንዳሉት ምርጫው አስቀድሞ የተጠናቀቀ መሆኑን ጋዜጣው በመጥቀስ የምዕራብ ፖሊሲ አውጪዎች እንዲህ ዓይነቱን ዝምታ በመምረጥ ከኢህአዴግ አፋኝ አገዛዝ ጋር መሞዳሞድ መቀጠላቸው የራሳቸውን አገር ብሔራዊ ጥቅም አደጋ ላይ እየጣሉት እንደሆነ ሊገባቸው በሚችል ቋንቋ አስረድቷል፡፡
የምዕራቡ ዓለም ሚዲያ ውጤቶች በኢህአዴግ ላይ ይህንን መሰሉ ትችት ሲያቀርቡ ይህ የመጀመሪያቸው አይደለም፡፡ እንዲህ ባለው አጭር ጊዜ ውስጥ ታዋቂ የሆኑ ጋዜጦች በተደጋጋሚ ኢህአዴግን ሲተቹ ግን በዓይነቱ የመጀመሪያው ነው ሊባል ይችላል፡፡ ከዚህ ቀደም አንድ የምዕራብ ሚዲያ በኢህአዴግ ላይ የሰላ ትችት ሲደርስ ኢህአዴግ “በእጅም በእግርም” በማለት በሌላ ተመጣጣኝ ሚዲያ የአጸፋ ምላሽ ሲሰጥ በተደጋጋሚ የተከሰተ እውነታ ነው፡፡ አሁን ግን ከአንድ ጊዜ በላይ ይህንን ዓይነት ተደራራቢ ትችት ሲቀርብበት ሊያስተባብልለት የሚችል ተመጣጣኝ ሚዲያ አለማግኘቱ ወይም ሞክሮ እምቢ መባሉ “የስሉሱን” መዞር እውነተኛነት የሚያጠናክር እንደሆነ አብሮ የሚጠቀስ ነው፡፡
በጥቂት ሳምንታት ውስጥ አራት የምዕራብ አገራት ታዋቂ ጋዜጦች ይህንን ዓይነት ዘገባ ማቅረባቸው የምዕራቡ ዓለም የፖለቲካ ዘዋሪዎች በኢህአዴግ ላይ አቋም እንዲወስዱ ተገቢውን ግብዓት በይፋ እየሰጡ እንደሆነ ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚችል እና ድርጊቱም ያለምክንያት እንዳልሆነ የፖለቲካ ተንታኞች የሚስማሙበት ሃሳብ ነው፡፡ በኢትዮጵያ በሚገኝ አንድ የትምህርት ተቋም የፖለቲካ ሳይንስ ምሁር የሆኑ ለጎልጉል ይህንን ጉዳይ ሲገልጹ “የምዕራብ ፖለቲከኞችና ጋዜጦች በቁርኝት ነው የሚሰሩት፤ ፖለቲከኞች የሚፈልጉትን ለማድረግ ሲፈልጉ በጋዜጦች በኩል ሃተታ እንዲሰራ ያደርጋሉ ከዚያ ያንኑ ዘገባ መልሰው እንደማስረጃ በመጠቀም የፖሊሲ ለውጥ ለማድረግ ይጠቀሙበታል፤ ሰሞኑን የምዕራብ ጋዜጦች እየወሰዱ ያለውን የተለየ አቋም ከዚህ አንጻር ከተመለከትነው በእርግጥ ምዕራባውያን በኢህአዴግ ላይ ስሉሱን ሊያዞሩ ነው እንዴ በሚል ሊታይ የሚችል ሲሆን ይህ አካሄድ ምን ያህል ለውጥ ሊያመጣ ይችላል የሚለው በሂደት የሚገለጽ ነው፤ በውጭ አገር ያለው ኢትዮጵያዊ የሚያደርገው ግፊትና ተጽዕኖም ከዚሁ ጋር በተዛማጅ ሊጠቀስ የሚገባው ነው” ብለዋል፡፡
የምዕራቡ ዓለም ጋዜጦች በኢህአዴግ ላይ የጀመሩት “ዘመቻ” ወደ የትኛውም አቅጣጫ ይሂድ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚታየው ሁኔታ ግን “ስሉሱ” ቢዞርም ባይዞር የሕዝቡ ምሬት ከምንግዜውም በበለጠ እየጨመረ መምጣቱን ነው፡፡ ሁኔታውን በቅርበት የሚከታተሉ ወገኖች የዕርቅን አማራጭ በተደጋጋሚ እያቀረቡ ያለ ቢሆንም ከኢህአዴግ በኩል የሚሰማው ግን “እንደጀመርን እንጨርሰዋል” የሚል ቀረርቶ ብቻ ነው፡፡
ፕ/ር መስፍን ወልደ-ማርያም “የወያኔ የጥላቻ ፍሬ” በሚል ርዕስ የዛሬ ዓመት አካባቢ ባወጡት ጽሁፍ ላይ እንደጠቆሙት ግፍ ማብቂያ እንደሚኖረውና አልሰማ የሚል ሁሉ ጊዜውን ጠብቆ በግድ እንዲሰማ እንደሚደረግ ይህም ደግሞ ለማንም እንደማይበጅ ሲገልጹ እንዲህ ብለው ነበር፡- “ወያኔ ከሀያ ዓመታት በላይ አፍንጫ እየያዘ ያስከፈለውን የሚመልስበት ጊዜ እየተቃረበ ነው፤ ጥያቄው ወያኔ እንዲመልስ የሚገደደው እንዴት ነው? የሚል ነው፤ ጥላቻ ወደ ንዴት፣ ንዴት ወደ ቁጣ ተለውጦ ሲገነፍል ምጽዓት ደረሰ ማለት ነው፤ ሁሉም ሰው ራቁቱን ይሆናል፤ አንደአውሬ ከጥፍሩና ከጥርሱ በቀር ሌላ መሣሪያ አይኖረውም፤ ሰው ሁሉ በክፋት ወደ አውሬነት ይለወጣል፤ ጠመንጃና ቦምብ አያገለግሉም፤ ሕንጻው ምሽግ አይሆንም፤ መኪናው፣ ባቡሩ፣ ታንኩ ከቆመበት አይነቃነቅም፤ የትም አያደርስም፤ ጭፍራ ሁሉ በየራሱ ፍዳ ታንቆ እንኳን ለሌላ ሊተርፍ ለራሱም የማይበቃ ይሆናል፤ ለነገሩ ጌታና ሎሌም የለም፤ ሁሉም በአውሬ እኩልነት የተፋጠጠ ነው፤ ርኅራኄ ተሟጦ፣ መግል ያዘለ ልብ ፈርጦ፣ ውይይትና ክርክር አብቅቶ፣ ጥርሱን ያገጠጠና ጥፍሩን የሳለ መንጋ በደም የሚራጭበት ሁኔታ ነው።”
በመጪው ግንቦት ወር ይካሄዳል ከሚባለው ምርጫ አኳያ ኢህአዴግ እየተጓዘበት ያለው የዕውር መንገድ፤ በልማትና ዕድገት ስም በሕዝቡ ላይ እየጫነ ያለው ቀንበር፤ “እኔ ከሌለሁ አገር ትፈርሳለች” የሚለው ቅኝት፤ በተቃዋሚዎች ላይ የሚያደርሰው ዓይን ያወጣ በደል፤ አፈና፣ እስራት፣ ግድያ፣ … የግፉን ሸክም እያገዘፈው ብቻ ሳይሆን የሚሄደው መሸከም የሚችል ወገብ እንዳይኖርም ያደርገዋል፡፡ የዚያን ጊዜ የግፉን ቀንበር ተሸካሚው መውደቁ የማይቀር ይሆናል፡፡ ይህ ሲሆን “ስሉሱ” ቢዞርም ባይዞርም አሸካሚው ግፈኛም ሚዛኑን ስቶ መውደቁ የማይቀር ነው፡፡

ወያኔና ሽብርተኛነት


terrorist-cat
ወያኔነትና ሽብርተኛነት ትናንት ምን ዓይነት ግንኙነት ነበራቸው? ዛሬ ምን ዓይነት ግንኙነት አላቸው?
ወደዚያ ከመሄዳችን በፊት የአሸባሪነት የተግባር መገለጫው ምንድን ነው? ብለን እንጠይቅ፤ አሸባሪነት፡-
• ያለውን የሥልጣን ሥርዓት የማፍረስ ዓላማ ያለው ነው፤
• ዓላማውን ለማሳካት ጉልበቱን የሚያፈረጥመው ከሥርዓቱ ጠላቶች በሚያገኘው፡–
• የመሣሪያ እርዳታ፣
• የእውቀት ድጋፍና ገንዘብ
• ዓላማውን ለማሳካት
o ሰዎችን ገድላል
o ያስራል፤ ያሰቃያል
o ይዘርፋል፤ ይቀማል፤
• ዓላማውን ለማሳካት
o ሃይማኖቶችንና ባህልን ያዳክማል፤
o የጥንት ታሪክ ማስታወሳዎችንና የቆዩ መጻሕፍትን ያጠፋሉ፤
o የፖሊቲካ እምነትን ያግዳል፤
o የመሰብሰብ ነጻነትን ይከለክላል፤
o የመደራጀት ነጻነትን ይከለክላል፤
o ሀሳብን የመግለጽ ነጻነት ይከለክላል፤
o ጉልበትን ወደሥልጣን ይለውጣል፤
• አንድ ዓላማ፣ አንድ እምነት፣ አንድ ሀሳብ፣ አንድ ዘዴ አንድ መንገድ በቀር ሌላው ሁሉ ይዘጋል፤ ይህንን ጥርነፋ የሚቃወም ሁሉ አሸባሪ ተብሎ ይታሰራል፤ የሲአይኤ ሰላይ ተብሎ ተሰቃይቶ ይሞታል፤
ከዚህ በላይ የተዘረዘረት በሙሉ የሽብርተኞች ወንጀሎች የሚባሉ ናቸው፤ እነዚህን እንደመመዘኛ አድርገን በአንድ በኩል ወያኔን፣ ከተፈጠረ ጀምሮ እስካሁን የሚያድርገውንና እያደረገ ያለውን በማስታወስ፣ በሌላ በኩል ከዚህ በታች የተዘረዘሩትና በሽብርተኛነት ተከስሰው በእስር ቤት የሚገኙት ሰዎችን
• እስክንድር ነጋ፣ ርእዮት ዓለሙ፣ ተመስገን ደሳለኝ
• የዞን ዘጠኝ በመባል የሚታወቁት ወጣቶች፣ (ማኅሌት ፋንታዬ፣ አጥናፍ ብርሃኔ፣ ኤዶም ካሣዬ፣ አቤል ዋበላ፣ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ተስፋ ዓለም ወልደየስ፣ ዘለዓለም )
• አንዱዓለም አራጌ፣ አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ሀብታሙ
• ሌሎች ከግንቦት ሰባት ጋር ንክኪ አላችሁ ተብለው የታሰሩት
ስናመዛዝን በሽብርተኛነት መመዘኛዎቹ ከብደው የሚታዩት የትኞቹ ናቸው? የአሸባሪነት የተግባር መግለጫ ተብለው በተዘረዘሩት ውስጥ ባሉት ዓላማዎችና መንገዶች የሚንቀሳቀሱት የትኞቹ ናቸው? ወያኔ ነው ወይስ የታሰሩት ሰዎች? ሽብርተኛ ተብለው ከታሰሩት ውስጥ ባንክ ሲዘርፍ የተያዘ አለ? እኔ አስከማውቀው የለም፤ ከወያኔ ውስጥስ ባንክ የዘረፈ አለ? ራሱ መለስ ዜናዊ በኩራት ነግሮናል! በሌሎች ወንጀሎችም ቢሆን ያው ነው፡፡
ተጨማሪ ማስረጃ የሚሆነው የዓለም የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ሁሉ በወያኔ በሽብርተኛነት የታሰሩት ሁሉ እንዲፈቱ እየወተወቱ በአንጻሩ የወያኔን የሰብአዊ መብቶችን መጣስ እያወገዙ ነው፤ ስለዚህ ጋዜጠኞችንና የፖሊቲካ ሰዎችን እየለቀሙ በሽብርተኛነት እየወነጀሉ በየእስር ቤቱ መወርወሩ አላዋጣም፤ አዝማሚያው እንደሚያሳየው የወያኔ ጸረ-ሽብርተኛ መምሰል ለሲአይኤም የሚሸጥ ሊሆን የሚችል አይመስልም፡፡
በዚያ ላይ ሽብርተኞች በኢራቅና በአፍጋኒስታን አድርገው የመን ገብተዋል፤ ከየመን ሶማልያ ቅርብ ነው፤ ኬንያን እየፈተሹት ነው፤ የሱዳን ትርምስ ሽብርተኞችን እንደሚጋብዝ ጥርጥር የለም፤ የናይጂርያው ወደሱዳን ሲጠጋ መፈናፈኛ ይጠፋል፤ በሽብርተኛነት የተከሰሰችው ኤርትራ ለመሸሸጊያ ትሆን ይሆን?
ጤናማ ሰው ሆኖ ሽብርተኛነትን የሚደግፍ ያለ አይመስለኝም፤ ዛሬ በኢራቅ የሚደረገውን በየቀኑ ስንመለከት ወደቤታችን አልተጠጋም ብለን ልንዝናና የምንችልበት ሁኔታ ላይ አይደለንም፤ በዋልድባና በበዙ ሌሎች ቦታዎች የኢትዮጵያ ቅርሶች አደጋ ላይ መሆናቸው ይሰማናል፤ ግን በአቅመ-ቢስነት በዝምታ እንመለከታለን፤ ይህንን የአዳፍኔ የፖሊቲካ አቅጣጫ ለመለወጥ የሃሳብ መለዋወጫ መድረክ የሚፈጥሩትን ወጣቶች ሁሉ በእስር ቤቶች እያጎሩ ነው፤ አዲስ የፖሊቲካ መድረክ እንፍጠር ብለው በሰላማዊ መንገድ የፖሊቲካ ትግል የጀመሩትን ሁሉ እያሰሩ ነው፤ በትግራይ ውስጥ አረና በትግራይ ያለውን የፖሊቲካ መሻገት ለማጥራት እንዳይሞክር እየተደረገ ነው፤ ከዚህ በፊት ገብሩ ዓሥራት የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ኅብረትን በክፉ የጭካኔ ዘዴ እንዳዳከመ አሁንም አረናን ለማዳከም እየተሞከረ ነው፡፡
መቼ ነው ወያኔዎችና ሎሌዎቻቸው ነገን የማየት ዓይኖች የሚያበቅሉት?

የኢትዮጵያ የ “ዲፕሎማቶች ቁንጮ” መሳለቅያ ቅጥፈት፣

የወባ ትንኝ ተመራማሪ የሆነ ሰው ስለዲፕሎማሲ ጥበብ እና ሳይንስ ምንድን ሊያውቅ ይችላል? ወይም ደግሞ እውነትን በመናገር እና ውሸትን በመናገር መካከል ያለው ልዩነት ምን ያውቃል? ወይም ደግሞ የለየለት ቅጥፈትን አምኖ በመቀበል እና ቅጥፈትን  በማውገዝ መካከል ያለውን  ልዩነት ምን ያውቃል? እነዚህ ሁሉ ጥያቄዎች ያለምክንያት አላነሰዋቸሁም፡፡
ቴዎድሮስ አድኃኖም በህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ውስጥ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር new፡፡ ይፋ በሆነው በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ የሕይወት ታሪክ አድኃኖም “ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያላው የወባ ትንኝ ተመራማሪ” መሆኑን ተገልጿል፡፡ አድኃኖም ከለንደን የጤና አጠባበቅ እና ትሮፒካል ህክምና ትምህርት ቤት/London School of Hygiene & Tropical Medicine የሰው ልጅ ሰውነት በሽታዎችን በመቋቋም ችሎታዎች/immunology ላይ ጥናት በሚያደርገው የተላላፊ በሽታዎች የህክምና ሙያ ላይ የማስተርስ ዲግሪ እንዲሁም ለንደን ከሚገኘው ከኖቲንግሀም ዩኒቨርስቲ እ.ኤ.አ በ2000 በህብረተሰብ ጤና/community health የዶክትሪት ዲግሪ ተቀብለዋል እየተባለ ይነገርለታል ፡፡ እ.ኤ.አ በ2005 አሁን በህይወት የሌለው መለስ ዜናዊ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር አድርገው ሾመው፡፡ እ.ኤ.አ በ2012 የመለስ ዜናዊን ህልፈት ተከትሎ አድኃኖም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነ ተሾመ፡፡ የወባ ትንኝ ተመራማሪ በአንድ ጊዜ ባንድ ሌሊት የጤና ጥበቃ ሚኒስትር በማግስቱ ጀንበር ሳይጠልቅ የሀገሪቱ ታላቅ የተባለውን የዲፕሎማትነት የስልጣን ቦታ መቆጣጠር የሚቻልበት የፖለቲካ ሂደት ሌላ የትም ሀገር ሳይሆን አች በወሮበላ ተቀሰፋ የተያዘቸው  የውሸቷ ሪፐብሊክ ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ ነው!
ውሸት በተንሰራፋባት ሀገር የቴዎድሮስ አድኃኖም 14 ዓመት ልጃገረድ መታለል፣
ባለፉት ጥቂት ሳምንታት በትውልድ ኢትዮጵያዊት በዜግነት አውስትራሊያዊት የሆነች እና ከየት ቦታ እንደመጣች የማትታወቅ የ14 ዓመት ልጃገረድ ከአድኃኖም ግን በመቀመጥ ቃለ መጠይቅ በማካሄድ እና በአውስትራሊያ አሸናፊ ሆና በሽልማት ያገኘችውን 20 ሚሊዮን ዶላር በኢትዮጵያ ለትምህርት ቤቶች ግንባታ አገልግሎት እንዲውል የለገሰች መሆኑን በገለጸችበት በዚያ የመድረክ ላይ ተውኔት አድኃኖም ዋና የገጸ ባህሪነት ድርሻን ይዘው ተውኔቱን ዋና ተጭዋች ነበር፡፡ አንድያው ለነገሩ ማንም የመታዘብ ቺሎታ ያለው ሰው እንደዚህ ያለ በህጻን ልጅ የሚደረግ  የሃያ ሚልዮን ዶላር ትረካ አውነት ብሎ ያምናል፡፡ በእርግጥ ባለፈው ህዳር worldnewsdailyreport.com የተሰኘ የቀልደኛ ድረ ገጽ አስርቱ ትዕዛዛት የተጻፉበት ጽላት በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ኃላፊዎች የተሰረቀ መሆኑን በመግለጽ ብዙ ኢትዮጵያውያኖች አስደንግጦና አሸብሮ ነበር።
በስደት ላይ የሚገኘው እና ሙሰኝነትን፣ አጭበርባሪነትን፣ የሀሰት ዲግሪዎችን እና በህወሀት ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ውስጥ ስልጣንን ከህግ አግባብ ውጭ የሚጠቀሙትን በማጋለጥ ታዋቂ የሆነው ወጣቱ የምርመራ ጋዜጠኛ አበበ ገላው እ.ኤ.አ መጋቢት 2/2015 አድኃኖም በአንዲት የትምህርት ቤት ልጅ የተታለሉ መሆናቸውን ምርመራ በማድረግ አንድ ዘገባ አዘጋጅቶ ነበር፡፡ [ማስታወሻ፡ በአድኃኖም የቅሌት ተውኔት ውስጥ የተሳተፈችውን የትምህርት ቤት ልጅ ሆን ብዬ ስሟን ይፋ ማድረግ አልፈልግም ምክንያቱም የልጅቷ ስም በመገናኛ ብዙሀን እንዲወጣ፣ እንድትወገዝ እና የስም ማጥፋት ዘመቻ እንዲፈጸምባት አልፈልግም፡፡ እንደዚሁም ደግሞ የ14 ዓመት የሆነች ልጅ ሙሉ በሙሉ በእራሷ ስብዕና የ20 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ዝርዝር የማጭበርበር ድርጊት በማውጣት ታታልላለች የሚል እምነት የለኝም፡፡ ከዚህ በኋላ ይህችን ልጅ ወጣቷ ወይዘሪት ወይም ደግሞ ልጅቷ እያልኩ እጠራታለሁ ምክንያቱም እርሷ እራሷ በአድኃኖም እና በግብረ አበሮቹ  አማካይነት ለርካሽ ፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ሲባል እንድትዋሽ የተደረገች የማጨበርበሩ ሰለባ ናትና ፡፡]
ከአድኃኖም ጋር ሲካሄድ በነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ወጣቷ እንዲህ ብላ ነበር፣ “በውድድር አሸናፊ ሆኘ 20 ሚሊዮን የአውስትራሊያ ዶላር በሽልማት አግኝቸ ነበር፡፡ እናም አሁን እዚህ የተገኘሁት ከኢትዮጵያ እና ከአውስትራሊያ መንግስታት ጋር በመሆን በሀገሬ የግንባታ ፕሮጀክት ለመጀመር ነው፡፡“ ቀሪውን የልጅቷን ትረካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የውጭ ጉዳይ አስፈጻሚ የሆነው ሰው እንዲህ በማለት ተናግሮላታል፡
“መታወቅ ያለበት አንድ ዋና ነገር ልጅቷ በአውስትራሊያ በሚገኙ ክለቦች ውስጥ ተሳትፎ በማድረግ ላይ የምትገኝ ልጅ ናት፡፡ እርሷ ከምትመራቸው ክለቦች ውስጥ አንደኛው የሰብአዊ መብት ጉዳዮች ጥበቃ ክለብ ነው፡፡ በዚያ ክለብ ውስጥ እርሷ እና ሌሎች የክለቡ አባላት ሌሎችን ሰዎች እንዴት መርዳት እንደሚችሉ ሀሳብ ይለዋወጣሉ፣ ውይይትም ያካሂዳሉ፡፡ እርሷ ያነሳቸው ዋነኛው ሀሳብ ሌሎቹ ትምህርት የማግኘት ዕድል እንዴት ማግኘት እንደሚችሉ ከማሰቡ ላይ ነው፡፡ በአውስትራሊያ ያሉ ህዝቦች ይህንን በሚሰሙበት ጊዜ ይህንን ሀሳቧን የደገፉ ሰዎች ገንዘብ አሰባስበው 20 ሚሊዮን ዶላር ለእርሷ ሰጧት፡፡ ይህ ድርጊት የተፈጸመው እ.ኤ.አ በ2014 ነው፡፡ ለጉብኝት ወደ ትውልድ ሀገሯ በመጣች ጊዜ ከእራሷ አንደበት እንደሰማችሁት በሽልማት ባገኘችው በ20 ሚሊዮን ዶላር በሀረር በጋራሙለታ አካባቢ ትምህርት ቤት ለመገንባት እንደምትፈልግ ሀሳቧን ገልጻለች፡፡ እንግዲህ ኃላፊነቱ ካላቸው ባለስልጣኖች ጋር በመተባበር በቅርብ ጊዜ ውስጥ ስራውን ትጀምራለች፡፡”
አንድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት አንዲትን የ20 ሚሊዮን ዶላር ተሸላሚ የሆነች ልጅ እንዴት አድርጎ ሊያውቅ እና ሊያገኛት ቻለ? ለዚህ ጥያቄ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ እንዲህ የሚል ገለጻ ሰጥቷል፡
ወጣቷ ልጅ በመጣች ጊዜ ስለእርሷ ማንነት የሚገልጹትን ሰነዶች ተመለከትን፡፡ ልጅቷ ወደ እኛ ቢሮ የመጣችው በቤተሰቦቿ አማካይነት ነው፡፡ የተከበሩት የእኛ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስለልጅቷ ጉዳይ አወቁ እናም ይኸ ጉዳይ ለሌሎች ወጣቶችም መልካም አርዓያ ስለሆነ ልጅቷን ማበረታታት እና ስለዚህ ጉዳይ መናገር አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡ ከዚህ አንጻር ሚኒስትሩ ጠንካራ በሆነ መልኩ ልጅቷን አበረታትተዋታል፡፡ ስለሆነም ልጅቷ ወደ እርሳቸው እንድትመጣ ጥሪ በማድረግ አነጋግረዋታል፡፡ መንግስት ማድረግ ያለበትን አስፈላጊውን ነገር ሁሉ ለማድረግ እና ለማገዝ ዝግጁ መሆኑን እንዲሁም ልጅቷ የምትፈልገውን እርዳታ ሁሉ እንደሚያደርግላት አረጋግጠውላታል፡፡   
ይኸ የ20 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ዋናው ችግር ገንዘቡ ፍጹም የሌለ እና ያልተገኘ የመሆኑ ጉዳይ ነው፡፡ ልጅቷ እንደዚህ ያለ ሽልማት በፍጹም አልተቀበለችም፡፡ ይህ ድርጊት ሙሉ በሙሉ ሸፍጥ ነው፡፡ አንድ የተከበረ ሚኒስትር የ8ኛ ክፍል ተማሪ የሆነች ልጅ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት ከአውስትራሊያ 20 ሚሊዮን የእርዳታ ዶላር በመያዝ ወደ ኢትዮጵያ ትጓዛለች ብሎ ማመን አንደ ማሞ ቂሎ አይነት ተረት ይመስላል ወይም ህዝብን አንዴ ሞኝ ከማየት የመጣ ይመስላል።
ይህንን አባባል በሌላ መልኩ ለማስቀመጥ የ20 ሚሊዮን ሽልማት ተብየው የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ባለፉት አስርት ዓመታት በኢትዮጵያ በየዓመቱ በአማካይ 11 በመቶ የምጣኔ ሀብት ዕድገት አስመዘገብኩ (በነገራችን ላይ ይህ አሀዝ የለየለት ሀሰት፣ ተራ ቅጥፈት እና የቁጥር ጨዋታ መሆኑን ከጥርጣሬ በላይ በማስረጃ አስደግፌ ያረጋገጥኩት ጉዳይ መሆኑን ልብ ይሏል) ከሚለው ማጭበርበሪያ ጋር አንድ አይነት እና ተመሳሳይ ነው፡፡ ሁለቱም ማጨበርበሮች በነባራዊ እውነታ ላይ የሌሉትን እንዳሉ አድርገው የሚያቀርቡ ላም አለኝ በሰማይ ወተቷን የማላይ የሆኑ የሸፍጥ አካሄዶች ናቸውና፡፡
የአበበ ገላው የምርመራ ዘገባ በአሰራር ስልት የአድኃኖምን የ20 ሚሊዮን አጠያያቂ ሽልማት ውድቅ አድርጎታል፡፡ አበበ የ20 ሚሊዮን ሽልማት በትምህርት ቤታችሁ ለምትማር ልጅ ሰጥታችኋል ወይ በማለት ልጅቷ ለምትማርበት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር  የስልክ ጥያቄ አቅርቦ ነበር፡፡ የትምህርት ቤቱ ርዕሰ መምህር እንዲህ የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፣ “ይኸ እንቆቅልሽ የሆነ ነገር ነው፣ ትምህርት ቤታችን እንደዚህ ያለ የ20 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ሰጥቶም፣ ውድድር አድርጎም አያውቅ፡፡ እንደዚሁም ደግሞ ልጅቷ ለ20 ሚሊዮን ዶላር የሚያበቃ እውቀትም የላትም፡፡“ አበበ በአውስትራሊያ በሜልቦርን የገንዘብ ማሰባሰቡን የማስተባበር ስራ አከናውኗል ከተባለው ባደን ፓወል ኮሌጅ ጋርም ግንኙነት አድርጓል፡፡ ኮሌጁ እንዲህ በማለት የማስተባበያ ቃሉን ሰጥቷል፣ “እንደዚህ ባለ አስገራሚ ጉዳይ ላይ መሳተፍ ይቅርና ኮሌጁ እራሱን የሚያንቀሳቅሰው 12 ሚሊዮን ዶላር በሆነው አመታዊ በጀቱ ነው፡፡“  በአውስትራሊያ የሮታሪ ዓለም አቀፍ ማናጀር የሆኑት ይህ ድርጀት ሽልማት ለመስጠቱ በአበበ ጥያቄ በቀረበላቸው ጊዜ በሀገሪቱ ውስጥ ያሉት ሁሉም ቅርንጫፎች በበጀት ዓመቱ ውስጥ 5.6 ሚሊዮን የአውስትራሊያ ዶላር ብቻ መሰብሰባቸውን እና በምንም ዓይነት መልኩ እንደዚህ ላለች የ14 ዓመት የትምህርት ቤት ልጅ 20 ሚሊዮን ዶላር መሸለምም ሆነ መስጠት አስደንጋጭ እና አሳፋሪ ነገር መሆኑን ግልጽ አድርገው ተናግረዋል፡፡
የአውስትራሊያ መንግስት ስለ20 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ምንም የሚያውቀው ነገር እንደሌለ እና ለኢትዮጵያ መንግስት ለትምህርት ተብሎ የተሰጠ ገንዘብ እንደሌለ ግልጽ አድርጓል፡፡ እንግዲህ ነገሮች ሁሉ እንደዚህ የሚሆኑ ከሆነ የ20 ሚሊዮን ዶላር ቅጥፈት ከየት መጣ?
እንደ አበበ ገለጻ ከሆነ ወጣቷ ልጅ ከአድኃኖም ጋር በካሜራ ተቀርጻ ለቴሌቪዥን የጋራ ጋዜጣዊ መግለጫ ከመቅረቧ ከሰዓታት በፊት በአድኃኖም እና በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቡድን እና በአማካሪዎች አማካይነት ውሸት እንድትናገር በመቅረጽ በቴሌቪዥን እንዲቀርብ እንዲደረግ የማግባባት ስራ ተደርጎላታል የሚል ግምት አለ፡፡ የተባለው ገንዘብ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የጭቆና አገዛዝ ተቀናቃኝ የሆነ ተቃዋሚ በሚንቀሳቀስበት በምስራቅ ኢትዮጵያ በጋራ ሙለታ አካባቢ ለትምህርት ቤቶች ግንባታ ይውላል መባሉ ለህዝብ ግንኙነት ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ዘግቧል፡፡ እንደ አበበ አስተያየት ከሆነ ሚኒስትሩ [አድኃኖም]፣ በተወልደ ሙሉጌታ የሚመራው የህዝብ ግንኙነት ቡድናቸው፣ በአውስትራሊያ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ እንዲሁም የኦሮሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦህዴድ) ባለስልጣኖች የኦሮሚያን ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አብዱላዚዝ መሀመድን ጨምሮ በዚህ አደገኛ የሆነ ቀውስን ሊያመጣ በሚችል የሸፍጥ ዕኩይ ድርጊት ውስጥ ተሳትፎ አድርገዋል፡፡
አበበ አንድ ጊዜ ታሪኩን ይፋ ማድረግ ከጀመረ በኋላ አድኃኖም ይህንን ድርጊት ለማስተባበል እ.ኤ.አ መጋቢት 7/2015 የማህበራዊ ድረ ገጻቸውን በመጠቀም በለቀቁት ጽሁፍ እርሳቸው በይፋ የዋሹትን ውሸት ልጅቷ አሳስታኝ ነው በማለት ውንጀላውን ሙሉ በሙሉ በልጅቷ ላይ ደፍድፈውታል፡፡ የአድኃኖም የማህበራዊ ድረ ገጽ ገለጻ በእውነታ ላይ ያልተመሰረተ ስለሆነ በጣም የሚያሸማቅቅ እና አሳፋሪ ጉዳይ ነው፡፡ ያቀረቡት አመክንዮ ውጤቱ እርባና የለውም በሚል ህግ ወይም መርህ ላይ በተመሰረተ የመጽሐፍ ምሳሌ እንዲህ በማለት ለማሳየት ሞክረዋል፡፡ አድኃኖም በአጠቃላይ ልጆች ትናንሽ ልጆችን ጨምሮ ጨዋዎች ናቸው የሚል አመክንዮ ለማቅረብ ጥረት አድርገዋል፡፡ ልጆች ይዋሻሉ፡፡ ልጆች የሚዋሹት ግን ከመጥፎ ድርጊት አስተሳሰብ በመነሳት ለክፋት ሳይሆን ከተራ ስህተት ነው፡፡ የልጆች የተሳሳቱ ውሸቶች ጨዋነት ያላቸው ውሸቶች ናቸው፡፡ ልጆችን አምናቸዋለሁ፣ ምክንያቱም የልጆች ውሸቶች ጨዋነትን የተላበሱ ውሸቶች ናቸው፡፡ እነርሱን ለማመን እመርጣለሁ፡፡ የልጆችን ጨዋነት የተሞላባቸውን ውሸቶች ማመን ስህተት ከሆነ ያንን ስህተት መፈጸምን እመርጣለሁ ብለዋል፡፡
አድኃኖም በማህበራዊ ድረ ገጻቸው እንዲህ የሚል የበከተ እና የበሰበሰ ሆኖም ግን በእርሳቸው አባባል ቅዱስነትን በተላበሰ መልኩ ለመጻፍ ሞክረዋል፡
“እንደምታውቁት ወጣቷ ልጅ ታዳጊ ልጅ ናት፡፡ ልጆች ምንም ዓይነት መጥፎ ነገርን የማይቀላቅሉ ጨዋዎች ናቸው በሚለው አባባል ላይ ከእኔ ሀሳብ ጋር ትስማማላችሁ የሚል እምነት አለኝ፡፡ ልጆች ስህተቶችን የሚሰሩ ከሆነ እነዚህ ስህተቶቻቸው ከመጥፎ ነገሮች የሚመነጩ ሳይሆን ከተራ ስህተቶች የሚመሰረቱ ናቸው፡፡ በዚህም ምክንያት ልጆች የሚነግሩኝን ነገር ሁሉ ለማመን እመርጣለሁ፡፡ ልጆችን ማመን ጥፋት ከሆነ ያንን ስህተት መስራቱን እመርጣለሁ፡፡ ስለሆነም አሁንም ቢሆን ይህችን ወጣት ልጅ ማመን እመርጣለሁ፡፡ ተገቢነት ያልሆኑ ነገሮችን በመጻፍ የልጅቷን ስሜት መጉዳት የለብንም፡፡  የእርሷ የፕሮጀክት ዕቅድ የተቀደሰ ነው፡፡ የእርሷ ፕሮጀክት ስኬታማ እንደሚሆን ጠንካራ የሆነ እምነት አለኝ፡፡ አሁን ዋናው ጉዳይ ይህችን ወጣት ልጅ ማበረታታት እና መደገፍ መቻል ነው፡፡
በእርግጥ የ20 ሚሊዮን ዶላር የሚባል ምንም ዓይነት ፕሮጅክት የለም፡፡ ሁሉም ነገር እውነት ሳይሆን ሸፍጥ ነው፡፡ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ለበርካታ አስርት ዓመታት ሲያደርግ እንደቆየው የ11 በመቶ የምጣኔ ሀብት ዕድገት የቅጥፈት የህዝብ ግንኙነት የፕሮፓጋንዳ ስራ ሲካሄድ እንደቆየው ሁሉ ነው፡፡ አድኃኖም በማህበራዊ ድረ ገጻቸው እንኳ ይኸ የ20 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት በተባለው በአንዲት የትምህርት ቤት ልጅ ፍጹም በሆነ መልኩ ተታልያለሁ፣ ተሞኝቻለሁ ወይም ደግሞ ተጭበርብሪያለሁ በማለት ለማመን የሞራል ድፍረቱ አልነበረዉም (በእርግጥ ይህንን መድረክ ላይ ተውኔት እራsu ያቀነባበሩት ካልሆነ በስተቀር)፡፡ ምናልባትም  በዚህ ጉዳይ ላይ ልንደነቅ አንችልም፡፡ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ባለፉት አስርት ዓመታት ሀገሪቱ በየዓመቱ በአማካይ በ11 በመቶ የምጣኔ ሀብት ዕድገት ስታስመዘግብ ቆይታለች ያለውን ተራ ወሸት፣ ቅጠፈት እና የቁጥር ጨዋታ ለመሆኑ እውቅና በመስጠት እንዲያምን እስከ አሁንም ድረስ ተስፋ ሳልቆርጥ በመጠበቅ ላይ እገኛለሁ፡፡
ወይ ጉድ!  ወይ ጉድ!
ከዚህ በላይ የተጠቀሰው አባባል ከህጻን ላይ ከረሜላ ነጥቆ እንደመውሰድ የቀለለ ተግባር ነው፡፡ አንድን የዲፕሎማሲ ቁንጮ የሆነን ታላቅ ባለስልጣን እና በቀጣይነትም የጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናል ተብሎ የሚጠበቅን ባለስልጣን አንዲት ህጻን የ20 ሚሊዮን ዶላር የሚከፋፈል ከረሜላ አለ በማለት የማታለል ወንጀል ተፈጽምበታለች ተብሎ ተሰምቶ አያውቅም፡፡ በፍጹም ሊሆን የሚችል ጉዳይ አይደለም! በጣም አስፈሪ የሆነው እውነታ ግን አድኃኖም በ14 ዓመት ልጅ የ20 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ታሪክ ትረካ በማቅረብ የሚታለል ከሆነ አስቸጋሪው እና ትልቁ ነገር ይህ ባለስልጣን ቀንድ ያለው ነገረኛ፣ ካገጩ ላይ ጺሙን ያንጨበረረ መሰሪ፣ ቀጣፊ ምላስ ያለው፣ ተናግሮ ማሳመን የሚችል አንደበተ ርትኡ የሆነ የዲፕሎማሲ ሰው፣ እምነተ ቢስ እና አጭበርባሪ የሆነ ሰው፣ ሁለት ምላስ ያለው፣ ሆን ብሎ ጓደኝነትን ክዶ የሚያጭበረብር፣ አንድን ነገር በማስመሰል የሚደብቅ፣ ጭልፊት የሆነ አታላይ የዲፕሎማሲ ሰው በሚያጋጥመው ጊዜ ምን ሊያደርግ ነው? እንዲያው ሁሉም ነገር በአንክሮ ሲታይ አሳዛኝ እና የሀገሪቱን መጥፎ ዕጣ ፈንታ በጉልህ የሚያመላክት ነገር ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ወኔን አጠንክሮ ቀበቶን ጠበቅ በማድረግ ትግሉን ማጧጧፍ የእያንዳንዱ ዜጋ በተለይም ተማርን ለሚለው ወገን ታላቅ ኃላፊነት ነው፡፡ የትግሉን ቀጣይነት እንዲህ በሚሉ የተቋጠሩ የግጥም ስንኞች ስንቅነት እድንይዘው ጀባ ልበላችሁ፡፡
በክቦቹ ዙሪያ እሩጡ ዘምሩ፣
ጽጌረዳ ያዙ ማንንም ሳትፈሩ፡፡
በኪስ ሙሉ አበባ በመያዝ እሩጡ፣
ከጫፍ እስከ ጫፉ ሳትበጣበጡ፡፡
ያ መጣ ብላችሁ ሀሳብ ሳይገባችሁ፣
ያ ሄደ ብላችሁ ጭንቀት ሳይዛችሁ፣
ሁላችሁም ለድል ለስኬት ብላችሁ፣
ጉዞውን ፈጽሙት ወገን እባካችሁ፡፡
ሩጫው በርትቶ ድካሙ ሳይዘው፣
እስትንፋስ ሳያጥረው ነጭ ላብ ሳይወርደው፣
ጉልበቱ በመራድ ሳይዛነፍ ወኔው፣
ሸሚዙን አውልቆ ሳይዝ በትከሻው፣
ትግሉን አጧጡፉት ለመልካም ፍጻሜው፡፡
የአድሃኖም ጋር የሚሰሩ የዲፕሎማሲ ሰዎች አሱን ለማታለል አጃቸዉን አየፈተጉ ለሀጭቻቸዉን አያንጠባጠቡ ከልጅ ከረሜላ አንደመወስድ ያህል አየጠበቁ ነው።
የኢትዮጵያ ቁንጮ የዲፕሎማሲ ሰው የሆነዉን አድኃኖም እንደዚህ ያለ ምንም ዓይነት ማገናዘብ የማይል የዋህ፣ በቀላሉ የሚታለሉ ወይም ደግሞ ብልህነት ያነሳቸው እና ነገሮችን ሰፋ አድርጎ የመመልከት ችሎታ የሌለው በመሆን አንዲት ልጅ ከቢሯቸው ድረስ ሰተት ብላ በመሄድ የ20 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ ልገሳ በመስጠት ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት የሚል የተዛባ እና እውነትነት የሌለው ትረካ በማቅረብ ልታታልለው ትችላለች? አድኃኖም እንዴት እንደዚህ በቀላሉ ሊታለል  ቻለ? የሀገር የዲፕሎማሲ ሰው መሆን ማለት ስለሀገር ሲባል በመሰረታዊ ጭብጡ ውሸትን እውነት አድርጎ የማቅረብ ሙያዊ ክህሎት መሆኑን እንዴት ማወቅ ተሳነው? ዲፕሎማሲ ለስልታዊ እና ዘለቄታዊ ጥቅም ሲባል እውነቱን ያለመናገር ክህሎት መሆኑን አልተገነዘቡምን? በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ ይህንን ጉዳይ ወደ ኋላ እመልሰዋለሁ፡፡ ውሸት በሚነገርባት በኢትዮጵያ ላይ ውሸት መዋሸት የኑሮ ስልት ነው፡፡
በእርግጥ አድኃኖም በእውነታው እና ባቀረቧቸው የክርክር አመክንዮዎች በእጥፍ ስህተት የሰራ ሰው ነው ፡ ህጻናት እንደ ማስመሰያ ጸጉር/ዊግ አይዋሹም፡፡ (ይህ ማለት ወጣቷ ልጅ በምንም ዓይነት መንገድ በዚህ የቅሌት ዕኩይ ተግባር ላይ ትዋሻለች ማለት አይደለም፡፡ ይልቁንም ይህንን የመሰለውን የማታለል ድርጊት መፈጻም እንድትችል የተቀነባበረ እና እንድትፈጽመው ስልጠና የተሰጣት ለመሆኑ ፍንጭ ሊሰጡ የሚችሉ ነገሮች ተንጸባርቀዋል፡፡)
ውሸትን ከእውነት ለመለየት ለምንሰራ ሰዎች ቢያንስ ከህግ ምርመራ ሁኔታዎች አንጻር ልጆች እንደ እርካሾቹ የቻይና ሰዓቶች የሚዋሹ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ እድሚያቸው ከሶስት ዓመታት በታች የሆኑ ህጻናት እውነትን ከውሸት ለመለየት አይችሉም፡፡ እስከ ሰባት ዓመታት ድረስ ጥቂት ልጆች በእውነታ እና በማገናዘብ ኃይል መካከል ያለውን ልዩነት የመገንዘብ   ይችላል፡፡ ጥቂት የሆኑ ነጭ ውሸቶችን መዋሸት ይጀምራሉ፡፡ በ10 ዓመታቸው እውነትን መናገር እና ውሸትን መናገር ምን ማለት እንደሆነ አሳምረው ያውቃሉ፡፡ እናም ውሸት በሚዋሹበት ጊዜ ፒኖክዮ እንደሚባለው እውነተኛውን ተናግሮ እንደ እውነተኛ ልጅ ለመሆን እንደሚሞክረው አሻንጉሊት የእንጨት ተክል ናቸው፡፡ በ10 ዓመታቸው በእርግጠኝነት ሲዋሹ እና እውነታውን ለጥጠው ሲናገሩ እንዲሁም ለስለስ ያሉ ውሸቶችን  እና ግማሽ የሆኑ እውነቶችን የመፈብረክ ችሎታን ያዳብራሉ፡፡ እንደዚሁም እውነትን አሳምሮ እና አጣፍጦ ከመናገርም በላይ በዝርዝር የቀረቡ እውነታዎችን እና ረዣዥም ትረካዎችንም ማቅረብ ይችላሉ፡፡
በ10 ዓመታቸው ልጆች ሙሉ ለሙሉ በሚዋሹበት ጊዜ ብቻ አይደለም የሚያውቁት እናም የ20 ሚሊዮን ዶላር ማጭበርበር በወጣቷ ልጅ ተፈጽሟል የሚለው ሁኔታ እ.ኤ.አ በ1979 የቀረበውን ተንቀሳቃሽ ህይወት አልባ አስቂኝ ፍጡር በዚህች ውሸት በሚነገርባት ምድር ላይ በመኖር ቶሎ ቶሎ የሚተነፍሰውን የውኃ ተርብ አስታወሰኝ፡፡ በዚያ የህይወት አልባ የምስል እንቅስቃሴ ላይ የሚተውነው ተርብ ሳንዲ የምትባለውን ትንሿን ልጃገረድ በኃይል አስገድዶ ወደ የውሸት ዓለም ወደሆነችው ምድር ላይ በመውሰድ ፒኖክዮ ከሚባለው ታዋቂ ተክል እና እንደ በሬ ወለደ ከሚለው ልጅ ዘንድ በመውሰድ እንድትገናኝ በማድረግ እንዲህ የሚል ቃለ ምልልስ ያደርጋሉ፡
ሳንዲ፡ ፑፍ፣ ተመልከት!
ፑፍ፡ እስከ አሀን ድረስ ማንም አይቷት የማያውቅ ቀይ እና ሰማያዊ ቀለም ያላት ላም ናት፡፡
ሳንዲ፡ እንደዚሁም ቀይ ቀለም ያለው ዝሆን
ፑፍ፡ ጥቂቶች ሁልጊዜ ያያሉ
ሳንዲ፡ ያ ማን ነው?
ፑፍ፡ ኪልሮይ፡፡ ሁልጊዜ እዚያ ነበር እናም የትም አልነበረም፡፡
ፑፍ፡ እኔ የውኃ ተርቡ የትምህርት ቤት የቤት ስራየን ምሳ አድርጌ መብላት እንደምችል ማሰብ አዲስ ነገር አይደለምን? በእርግጥም ከዚህ ቀደም ተደርጎ የማያውቅ አዲስ ነገር ነው፡፡ ውሸት ነገር ነበር፡፡ ቅሌት ነገር ነው፣ ትክክለኛ እና ታማዕኒነት ያለው መልስ መስጠት ያለመቻል ነበር፡፡ ኦ፣  ይኸ ነገር ሳንዲ በምትባል በትንሿ ልጃገረድ የተነገረ ቀላል የሆነ ውሸት ነበር፡፡
ሳንዲ፡ ፑፍ፣ ተመልከት!
ሳንዲ፡ የለም፣ እነዚህ ምዕናባዊ ውሸቶች ናቸው፡፡ እናም ጎጅ ያልሆኑ ምናባዊ ግንዛቤዎች ናቸው፣ እሺ፡፡ እናም ይኸ ነገር አስቂኝም ጭምር ነው፡፡
ለቴ እኔም ግማሽ የምናብ ግንዛቤ ነኝ፡፡
ወጣቷ ልጃገረድ ከአውስትራሊያ ውሸት ወደሚኖርባት ምድር ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ከአድኃኖም እና ከሸፍጡ ግብረ አበሮች ጋር የማታለል ድርጊት ጋር እንድትገኛኝ የተደረገች ይመስለኛል፡፡ ምንም በተጨባጭ የሌለውን እና ማንም ያላየውን ሽልማት 20 ሚሊዮን ዶላር ምዕናባዊ የሆነ ውሸት እንድትዋሽ ተነግሯታል፡፡ በ20 ሚሊዮን ዶላር የትምህርት ቤት ግንባታ የአስራአራት ዓመት ልጅ ታረጋለች ብሎ ማመን ቀይ ዝሆን አለ ብሎ ማመን ያህል ነው።
ሆኖም ግን በውኃ ተርቡ እንደተበላው የቤት ስራ ሁሉ 20 ሚሊዮኑ የአሸናፊነት የሽልማት ዶላር አይን ያወጣ ቅጥፈት ነው፣ ታላቅ ቅሌትም ነው፣ ቀጥተኛ እና እውነተኛ ያልሆነ መልስን በመስጠት እውነትን ለመቅበር የሚደረግ ደባ ነው፡፡ አድኃኖም እና ግብረ አበሮቹ ሽልማቱ ሙሉ በሙሉ ፈጠራ የነበረ መሆኑን አሳምረው ያውቁታል፡፡ ሆኖም ግን ወጣቷ ልጅ ስለዚህ ጉዳይ እንድትናገር አድርገዋል፡፡ አያውቁትም ሊባል የሚችለው እንዴት ነው? እንዴት? አንዲት ትንሽ የሆነች ልጅ ከመንገድ ገብታ  20 ሚሊዮን ዶላር ለትምህርት ቤት ግንባታ የሚውል ገንዘብ አለኝ በማለት የሀገሪቱ ቁንጮ ለሆነ የዲፕሎማሲ ሰው ስትናገር አንድ ምክንያታዊ የሆነ በዓለም ላይ የሚኖር ሰው ማድረግ ያለበት ምንድን ነው? ይህችን ህጻን ልጅ በቴሌቪዥን መስኮት እንድትቀርብ በማድረግ ህዝቡ ከእርሷ ለጋስነት ትምህርት እንዲወስድ መለፍለፍ ነው? ይህንን ፍጹም የተሳሳተ እና ምዕናባዊ የሆነ የገንዘብ ሽልማት ጉዳይ በማስመልከት ለአውስትራሊያ ኤምባሲ፣ ለአንደኛ ደረጃው ትምህርት ቤት፣ ለሮታሪ ክለብ እና ለባደን ፓወል ኮሌጅ በመደወል ለማረጋገጥ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ቢሮ ማድረግ የለበትም ?  በአንድ በስደት ላይ ያለ ጋዜጠኛ ይህንን የመሰለ ቅሌት ጥቂት የሆኑ የስልክ ጥሪዎችን በማድረግ ካጣራ እና ውሸት መሆኑን ካረጋገጠ የአድኃኖም ቢሮስ በተመሳሳይ መልኩ እንደዚህ ማድረግ ያልቻለው ለምንድን ነው? አንዲት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ የሆነች ህጻን ልጅ በመንገድ ሰተት ብላ በመሄድ አድኃኖምን ማታለል የምትችል መሆኑ ሲታይ ዝም ብሎ እንደ ተራ ነገር የሚታለፍ ጉዳይ አይደለም፡፡ የምርመራ ጋዜጠኛ አበበ ገላው እንዳቀረበው ዘገባ ይህ ጉዳይ ታላቅ የሆነ የውስጥ ተግባር ነው፡፡
አድኃኖም ምክንያታዊ ባልሆነ እና በተሳሳተ መልኩ በማህበራዊ ድረ ገጽ ያካሄደው ጫካውን የመደብደብ ከንቱ ጥረት በቁስል ላይ እንጨት መስደድ እንዲሉ ከመሆን ሌላ የሚፈይደው ነገር የለም፡፡ ፈላስፋነትን የተላበሰ በሚመስል ሆኖም ግን በቅጥፈት በተላበሰ አንደበት እንዲህ ብለው ነበር፣ “ልጆች በስህተት ይዋሻሉ፡፡ የልጆች ውሸቶች ጎጅዎች አይደሉም፡፡ ወጣቷ ልጅ ስህተት አትሰራም ወይም ደግሞ ጨዋነትን በተላበሰ መልኩ ልትዋሽ ካልሆነ በስተቀር ጎጅ ውሸት አትዋሽም፡፡ ቁንጮ በሆኑት የዲፕሎማት ሰው እና በግብረ አበሮቿ በተነገራት መሰረት ታላቅ የውሸት ትረካ ፈጽማለች፡፡ ውሸትን እንደ ጨዋነት አድርጎ አስመስሎ የሚያቀርበው እና ታዕማኒነትን ባጓደለ መልኩ ቅዱስ ሀሳብ እንደሆነ አድርጎ የሚያቀርበው የአድኃኖም እምነተቢስ የማህበራዊ ድረ ገጽ መልዕክት ጥረት የተንሻፈፈ እና  የግንዛቤ አድማሳችንን የሚፈታተን ከንቱ ስሌት ከመሆን ያለፈ ፋይዳ የለውም፡፡ ዋልተር ስኮት “በመጀመሪያ ደረጃ መዋሸት ስንጀምር ምን ዓይነት ድር ነው እያደራን ያለነው” በማለት ተናግረው ነበር፡፡
አድኃኖም 20 ሚሊዮን ዶላር ስለተባለው የሀሰት የተጭበረበረ ገንዘብ ሁኔታ በእርግጠኝነት ምንም ዓይነት ነገር ሊነግረን አልደፈረም፡፡ ስለዚያ ጉዳይ የሚያውቁት ነገር ከሌለ ሆን ብለው እራሱን ደንቆሮ አድርጎ ነውን? ሰውየው በገዥው አካል በብቸኝነት በተያዘው በህዝብ መገናኛ ብዙሀን ለኢትዮጵያ ህዝብ ስላስተላለፉት ስለ20 ሚሊዮኑ ዶላር ቅጥፈት ኃላፊነቱን አልወሰደም፡፡ አድኃኖም እንደዚህ ባለ መልኩ ስለተፈጸመው ታላቅ ቅሌት ምርመራ እንዲደረግበትም እንኳ ትዕዛዝ አላስተላለፈም ፡፡ መግለጫዎችን አዘጋጅቶ በማቅረብ ሁኔታውን ለማረም እና በብዙሀን መገናኛ እንዲተላለፍ ምንም ዓይነት ጥረት አላደረገም፡፡
የበለጠ አስደንጋጩ እውነታ ደግሞ ህጻኗን ልጅ በሰይጣን እና በጥልቅ ሰማያዊ ባህር መካከል ጥለው ምንም ዓይነት ኃላፊነት ያለመውሰዱ ጉዳይ ነው፡፡ ይህች ህጻን ልጅ በጓደኞቿ እና አታላዩዋ ልጅ፣ አሳዛኟ ወንጀለኛ እና አጭበርባሪዋ ልጅ እየተባለች በመጥፎነት ስትታወስ  የምትኖር ስለመሆኗ አድኃኖም ጉዳዩ አይደለም፡፡ አድኃኖም ልጅቷን ከፈጣን አውቶብስ ስር በመጣል በጠቅላላ በ20 ሚሊዮን ዶላር ቅሌት ጋር በተያያዘ ለተፈጠረው ቸግር ሁሉ ሙሉ ኃላፊነቱን እንድትወስድ አድርገዋል፡፡ ልጅቷን ከመረጃ የትችት ማዕበል ውስጥ ጥለዋት ሄደዋል፡፡ እንደዚህ ያለ የጫካ ቅሌትን በማደራጃት እና በመምራት ለሰሩት ግፍ ይህችን ወጣት ልጅም ሆነ የኢትዮያን ህዝብ ይቅርታ አልጠየቀ ም፡፡ ወጣቷ ልጅ ጨዋነትን የተላበሰ እና ምንም ዓይነት ጉዳትን ሊያስከትል የማይችል ውሸት እንደዋሸች አድርጎ በመፈረጅ ይህንን ታላቅ ቅሌት እንደ ቀላል ነገር ለበስ ለበስ አድርጎ ለማለፍ ጥረት ተደርጓል፡፡ እንደዚህ ዓይነቱ ሁኔታ ሰዎችን ሆን ብሎ ለመጉዳት ዕኩይ ምግባር ለሚያራምድ ሰው፣ ቁንጮ ዲፕሎማት፣ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ከመቅጽበት ለይስሙላ ተቀምጦ ያለውን ጠቅላይ ሚኒስትር በማስወገድ የጠቅላይ ሚኒስትርነት ቢሮን ለመውሰድ ዙፋኑን እያሟሟቀ ላለ ባለስልጣን ምን ይባላል?
የሞራል ተቀባይነት በሌለው በአድኃኖም ባህሪ እጅጉን ደንግጫለሁ እናም አዝኛለሁ፡፡ ይህ የአድኃኖም ድርጊት ለኢትዮጵያ ህጻናት እና ለወጣቱ ትውልድ የሚያስተላልፈው መልዕክት ምንድን ነው? ለእነዚህ የህብረተሰብ ክፍሎች ምን ዓይነት ምሳሌነት ነው እያስቀመጡ ያሉት? ልጆች፣ እሺ ይሁን ይዋሹ ምክንያቱም በምትዋሽበት ጊዜ ስህተት እየሰራህ ነው፡፡ ውሸቶች ጨዋነትን የተላበሱ እስከሆኑ ድረስ ተገቢ ናቸው በማለት ለልጆች እየተናገሩ ነውን? የ20 ሚሊዮን ዶላር ጨዋ ውሸቶች የሞራል ዝቅጠት እና ስህተት የለባቸውም ምክንያቱም ልጆች መታመን አለባቸው በማለት እያስተማሩ ነውን? ለኢትዮጵያ ወጣቶች ምን ዓይነት አርዓያነትን ነው በማስተማር ላይ ያሉት? አድኃኖም የዚህን አዋራጅ ቅሌት ጉዳይ ከኢትዮጵያ ህጻናት ልጆች እና ወጣቶች አመለካከት አንጻር ተመልክቶታልን? ወጣቷ ልጅ ለኢትዮጵያ ወጣቶች ተምሳሌት ቀንዲል እንድትሆን አድኃኖም ጽኑ ፍላጎት አድሮበታል፡፡ የ20 ሚሊዮን ዶላር ሽልማት ጉዳይ ቅሌት መሆኑ በአደባባይ እየታየ እና በህዝብ ዘንድ እየታወቀ በአድኃኖም በኩል ወጣቷ ልጅ ምን ዓይነት የተምሳሌትነት ቀንዲል እንድትሆን ነው የተፈለገው? አድኃኖም የፈጠሩት የተምሳሌትነት ቀንዲል በአሁኑ ጊዜ የተዋረደ እና በቅሌት የተዘፈቀ አጭበርባሪነት ተብሎ የተወገዘ ስለመሆኑ ደንታ አላቸው እንዴ?
አድኃኖም ስለሞራል ስብዕና አመክንዮ ችሎታ አላቸውን? ልጆች እንደልጅነታቸው መዋሸታቸው ስህተት የለውም ብለን ብናምንም እንኳ እንደ አዋቂ ሰው መዋሸት ስህተት የሚሆነው ለምንድን ነው? በእርግጥ ውሸት እና ሸፍጥ በተንሰራፋበት ምድር መዋሸትም ፍጹም ተገቢ ነው የሚለው አባባል ትክክል ነው፡፡ ይቅርታ ሊደረግለት የማይችለው እና በምንም ዓይነት መልኩ ተቀባይነት የሌለው ነገር ግን አሁን በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው የዲፕሎማሲ ሰው ከህዝብ ነቀፌታ፣ ከቅሌት እና ውግዘት እራሳቸውን ለመከላከል በማሰብ ውሸት ጨዋነትን የተላበሰ ስህተት ነው በማለት ጉንጭ አልፋ እና አመክንዮ የሌለው ክርክራቸውን የመቀጠላቸው ጉዳይ ነው፡፡ ካፈርኩ አይመልሰኝ መሆኑ ነው እንጅ በምንም ዓይነት መንገድ ቢሆን ውሸት ውሸት እንጅ መቸውንም ጊዜ ቢሆን ውሸት ጨዋ ሊሆን አይችልም፡፡ ኢትዮጵያዊ ባህላችንም አይደለም አድኃኖም ሊበርዝብን ካልሆነ በስተቀር፡፡ ስህተት በነጠረ እውነት እንጅ በእራሱ በስህተት አይታረምም፡፡ እንደዚሁም ሁሉ ጨዋ ውሸት ያው ውሸት እንጅ በፍጹም ጨዋነትን ሊላበስ አይችልም፡፡ ስለሆነም በሀገር ላይ እየተሰራ ያለው ደባ እና ሸፍጥ በምንም ዓይነት መልኩ ይቅርታ ሊደረግለት የማይገባ የሞራል ስብዕና ወንጀል ነው፡፡
የሞራል ሰብዕና መሪዎች ወጣቶች እንዲዋሹ በፍጹም አያደፋፍሩም ወይም ደግሞ ውሸትን ታላቅ ቅሌት እንጅ የደግ ነገር ተምሳሌት ነው ብለው አቃልለው አይመለከቱም፡፡ የሞራል ሰብዕና መሪዎች ወጣት ውሸታሞች ውሸትን እንዲፈበርኩ ትዕግስቱ የላቸውም ወይም ደግሞ ጨዋ ዋሾች በማለት ይቅርታ አያደርጉላቸውም፡፡ የሞራል ሰብዕና መሪዎች በስህተት ነው ውሸት የተነገረው ለሚለው ምንም ዓይነት ይቅርታ የላቸውም፡፡ አንድ ህጻን የቤት ስራውን ወይም ስራዋን ባለማከናወኑ/ኗ ምክንያት የቤት ስራውን ውሻው በላው በማለት መዋሸት የለበትም/የለባትም፡፡ እንደዚሁም ሁሉ አንድ መንግስታዊ የሆነ ተቋም በእርግጠኝነት ውሸት፣ ተራ ቅጥፈት እና የቁጥር ጨዋታ መሆኑን አስረግጦ እያወቀ ባለሁለት አሀዝ የምጣኔ ሀብት ዕድገት አስመዝግበናል በማለት መዋሸት በምንም ዓይነት መልኩ ትክክል አይደለም፡፡ ልጆቻችን ሀቀኞች፣ የተከበሩ፣ ሞገስን የተላበሱ፣ ላመኑበት ዓላማ ጽኑዎች እና ግልጾች እንዲሁም ታማኞች እንዲሆኑ እነዚህን መሰረታዊ እሴቶች በቤት እና በትምህርት ቤቶች እንዲማሩ እናደርጋለን፡፡ እንደዚህ ዓይነቶቹ የሞራል ስብዕና እሴቶች በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ምድር ውስጥ ቦታ የላቸውም፡፡
በተደጋጋሚ ስናገረው እንደቆየሁት የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ አመራሮች የሬክ/የጀርመን የፕሮፓጋንዳ ሚኒስትር የነበሩትን የጆሴፍ ጎቤልስን እንዲህ የሚለውን መርህ አበርትተው ይከተላሉ፣ “ታላቅ ውሸት ከዋሸህ እና ይህንኑ ውሸት ደግመህ ደጋግመህ ከፈጸምከው በመጨረሻው ጊዜ ህዝቦች ማመን ይጀምራሉ፡፡ ውሸቱ ተደጋግሞ የሚነገረው መንግስት በህዝቡ ላይ ከተነሳበት የፖለቲካ፣ የምጣኔ ሀብት እና/ወይም ወታደራዊ የውሸት ውጤቶች በህዝብ ከሚወሰዱ እርምጃዎች እራሱን ለመደበቅ ሲል ብቻ በዚያን ጊዜ የሚፈጽመው ድርጊት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት መንግስት ያለውን ኃይል ሁሉ በመጠቀም ሰላማዊ አመጸኞችን ለመጨቆን፣ እውነት ዋና የውሸት ጠላት በመሆኗ እና ከዚህም በመነሳት እውነት ዋነኛ የመንግስት ቀንደኛ ጠላት ስለሆነች ውሸትን እንደ በቀቀን መድገም እና መደጋገም አስፈላጊው ነገር ነው፡፡“
አድኃኖም እና የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ሆን ብሎ እንደ በቀቀን ደግሞ እና ደጋግሞ የመዋሸትን የጎቤልን ትምህርት ወደ ላቀ እና ከፍ ወዳለ ደረጃ አሸጋግረውታል፡፡ የ20 ሚሊዮን ዶላር ውሸትን በመፈብረክ ውርርድ ገብተው ነበር፡፡ ሆኖም ግን ይህንን ውርርድ በጽናት በሚታገለው መርማሪ ጋዤጠኛ አበበ ገላው ሙያዊ ክህሎት ተራ ቅጥፈት ሆኖ በመገኘቱ ውርርዳቸውን አጥተዋል፡፡ ውርርዱን ማጣት ብቻም ሳይሆን በቅሌት ባህር ውስጥም ተዘፍቀው በመንቦጫረቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ላለፉት አስርት ዓመታት ስለኢትዮጵያ ባለሁለት አሀዝ የምጣኔ ሀብት ዓመታዊ ዕድገት ታላቅ ቅጥፈትን ፈጽመዋል፣ ሆኖም ግን የለየለት ውሸት መሆኑ በማስረጃ የተረጋገጠ በመሆኑ ተይዘዋል፡፡ ስለሆነም እነርሱ ሊቃወሙት የማይፈልጉት እንዲህ የሚል ስጦታ ልሰጣቸው እፈልጋለሁ፡ ስለባለሁለት አሀዝ የምጣኔ ሀብት ዕድገት፣ ስለ 20 ሚሊዮን ሽልማት፣ ምርጫዎች የሚዋሹትን ታላቅ ውሸት የሚያቆሙ ከሆነ እና ሌሎች በየሳምንቱ አዳዲስ ተራኪ ቅጥፈቶችን ከመፈብረክ የሚታቀቡ ከሆነ እኔም እንደዚሁ በየሳምንቱ ሰኞ እውነታውን በማውጣት ስለእነርሱ ቅጥፈት የምዘግበውን አቆማለሁ!
የወያኔ የቅጥፈት ዲፕሎማሲ እና ዋና የዲፕሎማት ሰው፣
የአድኃኖምን ድፍረት የተቀላቀለበት የዲፕሎማሲ አካሄድ እስከ አሁን ድረስ ተከታትያለሁ፡፡ በቪዲዮ የተቀረጸውን እና ለህዝብ የቀረበውን ተመልክቻለሁ፡፡ እናም እሱም ያደረገዉን ንግግር በማነብበት ጊዜ ማመን ተስኖኝ እራሴን በመያዝ አግራሞቴን ገልጫለሁ፡፡ የሀሳብ ምጥቀት ዳህራቸው ቅርብነት አስደንጋጭ ነው፡፡ የሚያደርጓቸው ንግግሮች ምንም ዓይነት ጥቅም እና ፋይዳ የሌላቸው በመሆናቸው ጥራት ይጎድላቸዋል፣ እንደዚሁም ደግሞ የነገሮች ተያያዥነት የላቸውም፡፡ እጅግ በጣም ውስብስብ የሆኑ ጉዳዮችን መልክ ለማስያዝ  በተማሪዎች እንቅስቃሴ ወቅት ሲነገሩ የነበሩ አሁን ጊዜ ያለፈባቸውን እና የቀሩትን ቃላት እና ሀረጎችን በመጠቀም አሁን በህይወት የሌሉትን አለቃቸውን ለመምሰል ይታትራሉ፡፡ ዓለምአቀፍ ዲፕሎማሲን በማወቅ በኩል በጣም አናሳ የሆነ ግንዛቤ አላቸው፡፡ አጅግ በጣም መሰረታዊ የሆኑ የዓለም አቀፍ ህጎች፣ ውሎች እና ስምምነቶች እውቀት ግንዛቤ እና መጠነኛ የሆነ ዕውቀት አንኳ ያላቸው ለመሆናቸው ምንም ዓይነት ማረጋገጫ አያሳዩም፡፡ ያቀረብኳቸውን ነጥቦች ተጨባጭ ለማድረግ አስረጅ ምሳሌዎችን እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡
1)  የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት/ICC በኡሩ ኬንያታ እና በዊሊያም ሩቶ ላይ መስርቶት ከነበረው ክስ ጋር በተያያዘ መልኩ፣
የኬንያ ፕሬዚዳንት በሆኑት በኡሁሩ ኬንያታ እና በእርሳቸው ምክትል በሆኑት በዊሊያም ሩቶ ላይ የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት ክስ መስርቶባቸው እ.ኤ.አ ለጥቅምት 2013 ተይዞ ለነበረው ቀጠሮ ቅድመ ዝግት ለማድረግ እና ክሱ እንዲቋረጥ ወይም እንዲራዘም ለማድረግ በማሰብ የአፍሪካ ህብረት አዲስ አበባ ላይ አድርጎት በነበረው ጉባኤ ላይ አድኃኖም ቀንደኛ አስተባባሪ በመሆን በሁለቱ ተጠርጣሪዎች ላይ የተመሰረተው ክስ ካልተቋረጥ የአፍሪካ ሀገሮች በሙሉ የሮማን ስምምነትን በመርገጥ በጅምላ ጥለው እንዲወጡ ሲያስተባብር ነበር፡፡ በአፍሪካ ህብረት ልዩ ጉባኤ የመክፈቻ ስነስርዓት ላይ በመገኘት አድኃኖም እንዲህ የሚል ንግግር አሰምቶ ነበር፡
የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት አፍሪካን እና አፍሪካውያንን ኢላማ በማድረግ እራሱን ወደ ፖለቲካ መሳሪያነት አሸጋግሯል፡፡ ይህ ዓይነቱ ትክክል እና ፍትሀዊ ያልሆነ አያያዝ ፍጹም ተቀባይነት የለውም፣ እናም ለዚህ ነው በICC ላይ ያለንን ስጋት ስንገልጽ የቆየነው…የኬንያን ፕሬዚዳንት እና ምክትላቸው ህገ መንግስታዊ ግዴታዎችን እና ኃላፊነቶችን ለመወጣት እንዲችሉ የራሳቸውን ስብሰባ እንዲመርጡ ፍርድ ቤቱ እንዲፈቀድላቸው ያቀረብነውን ጥያቄ አዎንታዊ ምልሽ አላገኘም…ኬንያን እና አህጉራችንን የሚበጠብጥ እንደዚህ ያለ የተጠርጣሪ/ሰለባ ዓይነት አቀራረብ አንፈልግም…የመንግስታት ርዕሰ ብሄሮች ሊከሰሱ አይችሉም እና ያለመከሰስ ከለላ አላቸው በሚሉ ጉዳዮች ላይ ግልጽ የሆኑ ውሳኔዎችን ይዘን መውጣት ይኖርብናል…ይኸ ጉዳይ በኬንያ እና በአጠቃላይ በአፍሪካ ላይ ትልቅ የሆነ መዘዝ ሊያመጣ የሚችል ለመሆኑ የሚያጠራጥር ነገር አይደለም… ምናልባትም ይህ ጉዳይ በICC እንዴት መያዝ እንዳለበት ወደፊት አፍሪካ ከICC ጋር በሚኖራት ግኙነት ላይ ጠንከር ያለ እንደምታ ይኖረዋል… ICC በእንደዚህ ያለ ሁኔታ በአፍሪካ እና በአፍሪካውያን ላይ የበላይነቱን እያሳዬ መኖር እዲቀጥል መፍቀድ የለብንም፡፡
በጉባኤው የመዝጊያ ስነስርዓት ንግግር ላይ አድኃኖም በባዶው የድል አድራጊነት መንፈስን በተላበሰ መልኩ ተኩፍሰው ታይቷል፡፡ በሮም ስምምነት መሰረት ሁሉንም የአፍሪካ ህብረት አባል ሀገሮች አሳድመው ከICC አባልነት በጅምላ እንዲወጡ ሊያደርጉት የነበረው ዕቅዳቸው ሙሉ በሙሉ ከሸፈበት፡፡ ሆኖም ግን እንዲህ በማለት ንግግሩን ቀጥሎ ነበር፡
ICC ዓለም አቀፍ የፍትህ አገልግሎቱን ለመስጠት ሲል የሚጠቀማቸውን የአድልኦ አሰራሮች ውድቅ አድርገናል፡፡ እንደዚሁም ICC በአፍሪካ በተመረጠ መልኩ በአድልኦ የሚፈጽማቸውን ተግባራት ግልጽ በሆነ እና በማያሻማ መልኩ የተሰማንን ቅሬታ ግልጽ አድርገናል፡፡ በተለይም ለመጀመሪያ ጊዜ በመንግስት ርዕሰ ብሄር እና በምክትላቸው ላይ በተመሰረተው የICC ክስ በጣም የተጎዳንበት እውነታ መፈጠሩን እና ይህም ሁኔታ የኬንያን ሉዓላዊነት የተዳፈረ መሆኑን ያመላክታል…
የኬንያታን እና የሩቶን በICC ከመከሰስ ጉዳይ ጋር በተያያዘ መልኩ አድኃኖም በሰጠው ትንታኔ ላይ የፍሬ ነገር ጭብጥ፣ የሕግ እና የአመክንዮ ግድፈት ይስተዋላል፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ የዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት አፍሪካን እና አፍሪካውያንን ኢላማ በማድረግ እራሱን ወደ ፖለቲካ መሳሪያነት አሸጋግሯል የሚለው የአድኃኖም ፍረጃ ይህ ድርጊት እውነት ስለመሆኑ ቅንጣት ያህል ማስረጃ ማቅረብ አይችልም፡ ICC በአፍሪካ እና አፍሪካውያን ላይ የበላይነትን በማሳየት አድሎአዊ አሰራርን ያራምዳል ለሚለው ውንጀላ ተራ አሉባልታ ካልሆነ በስተቀር በተጨባጭ ምንም ዓይነት የቀረበ ማስረጃ የለም፡፡ ምንም!
አድኃኖም ተጨባጭነት ያለው እና በማስረጃ እና በሕግ በተደገፈ አሰራር ሳይሆን ማሸነፍ የፈለገው የICCን ስም በማጥፋት እና ጥላሸት በመቀባት ነው፡፡ አድኃኖም በአፍሪካ እና በአፍሪካውያን ላይ አስቀድመው ያለምንም ማስረጃ የእራሱን ሀሳብ በመጫን እና የእርሳቸውን ሀሳብ እንዲቀበሉ ጥረት በማድረግ የሌሎች ሰዎች ስሜቶች እንዲጎዱ አድርገዋል፡፡ እንዲሁም በአድኃኖም እምነት መሰረት የነጮቹ የICC ዳኞች እና አቃብያነ ሕጎች የእነርሱን የዱሮውን የቅኝ አገዛዝ ስርዓት በICC አማካይነት በአፍሪካ እና በአፍሪካውያን ላይ ለመጫን ጥረት እያደረገ ነው በማለት ሌሎችም በስሜታዊነት የእርሱን በማስረጃ ያልተደገፈ ውንጀላ በመከተል ተንጋግተው እንዲወጡ ለማድረግ ጥረት አድርግዋል፡፡ እውነታው ግልጥልጥ እና ፍርጥርጥ ብሎ ሲታይ ግን በሚገዟት ሀገር በአሁኑ ጊዜ እየተገበሩት እንዳሉት ሁሉ ልምዳቸውን ከፍ በማድረግ በአፍሪካ በአሁጉር ደረጃ የዘር ካርድን ነቅሶ በማውጣት ነጮቹን የICC ሰዎች አሳፍረው እና አሸማቅቀው ለማባረር ያደረጉት የህጻን ዓይነት ጨዋታ እራስን ከትዝብት ላይ ከመጣል በስተቀር አንድም የፈየደው ነገር አልነበረም፣ ሊኖርም አይችልም፡፡
ዘረኝነትን አህጉር አቀፍ ለማድረግ ያደረጉት ያልተሳካ ሙከራ በአጫፋሪዎቻቸው ዘንድ ሊደገፍ ካልሆነ በስተቀር በሌላ በማንም የሚያስብ አዕምሮ ባለው ሰው ዘንድ የሚታሰብ ጉዳይ አይደለም፡፡ እውነታው ግን ICC እንደ እራሱ በጎጥ እና በመንደር የጠባብነት የዘር ስሜት የሚነዳ ሳይሆን በዘር፣ በመልክዓ ምድር እና በጾታ ህብረ ውህድ ያለው ለሰው ልጆች ሁሉ ሰብአዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንዲከበሩ፣ ፍትህ በዓለም ላይ ሁሉ እንዲሰፍን የሚታገል ዓለም አቀፋዊ ድርጅት ነው፡፡ በእርግጥ የእርሱ የይስሙላ አለቃ የሆነው ኃይለማርያም ደሳለኝ ICC ዘር አዳኝ ነው በማለት በይፋ በአደባባይ ተናግሮ ነበር፡፡ በዚያ ንግግር እኔ በግሌ በጣም ነው ያፈርኩት እና ውርደት የተሰማኝ፡፡ ከድፍን 60 ዓመታት የነጻነት ህይወት በኋላ የአፍሪካ መሪዎች የዘር ካርድን እየመዘዙ ማውጣቱን ስራዬ ብለው ተያይዘውታል፡፡ ምን ዓይነት የወረደ አሳፋሪ ድርጊት ነው!
እንደዚሁም ደግሞ ICC በማንኛውም የአፍሪካ ተጠርጣሪ ላይ አግባብነት የሌለው ድርጊት ለመፈጸሙ እና ፍትሀዊነት የጎደለው አሰራር ለመስራቱ ከመወንጀል በስተቀር ምንም ዓይነት ማስረጃ የለም፡፡ የአድኃኖም ድብቁ የክርክር ጭብጥ ግን ICC አፍሪካን እና አፍሪካውያንን በሰብአዊ መብት ወንጀሎች ይከሳቸዋል ምክንያቱም ጥቁር ስለሆኑ ነው የሚል አራምባ እና ቆቦ ሆኖ ይገኛል፡፡ የተከበሩ አድኃኖም ለመሆኑ አፍሪካውያን በዘር በICC ክስ ይመስረትባቸዋል ከተባለ በዘር ተከሰሱ እንዳይባሉ ንጹሀን ህዝቦችን ይፍጁ፣ ዕልቂት ይፍጠሩ፣ ያውድሙ እንደፈለጋቸው ይሁኑ እንዲባል ነው ፍላጎቱ? ወይስ ደግሞ ይህ የአምባገነንነት ሰይጣናዊ አስተሳሰብ የተጠናወተው የአፍሪካ ጥቁር ወሮበላ ዘራፊ በጠብመንጃ አፈሙዝ ስልጣንን እየጠቆጣጠረ እንደፈለገው በህዝቦች ላይ እልቂትን እየፈፀመ ሀብት እና ንብረታቸውን እየቀማ ባለበት ሁኔታ በዓለም አቀፍ ሕግ መሰረት ላጠፋው ጥፋት ተጠያቂ ይሁን መባሉ ለአፍሪካ ሲሆን እንዴት በዘር ነው ሊባል ይችላል?
ነጭ የቆዳ ቀለም ያለው ሰውም ቢሆን ሰብአዊ መብትን እስከደፈጠጠ ድረስ ከተጠያቂነት አያመልጥም፡፡ ይኸ ነገር የዘር እና የቆዳ ጉዳይ አይደለም፡፡ በርካታ መብት ደፍጣጮች በአፍሪካ ውስጥ የመገኘታቸው ሁኔታ እውነት ነው፣ ስለዚህም በርካታዎቹ ወይም ደግሞ ሙሉ በሙሉም ቢባል ወንጀለኞች እስከሆኑ ድረስ የአፍሪካው አምባገነኖች በህግ መጠየቃቸው ከዘር ጋር የሚያገናኘው አንድም ነገር የለም፡፡ አድኃኖም ወይም ደግሞ በዚህች መከራዋ ባላለቀላት ሀገር መሰረትሁት እንዳሉት የዘር የፖለቲካ ዥዋዥዌ ጨዋታ ሁሉ እንደ ብሄር ብሄረሰቦች የይስሙላ በዓል አከባበር እንደምታደርጉት ሌሎች ወንጀል ያልሰሩትን አህጉሮች ሁሉ በመጨመር በኮታ ከአፍሪካ፣ ከአሜሪካ፣ ከኢስያ፣ ከአውሮፓ፣ ከላቲን አሜሪካ፣ ከአውስትራሊያ….ይህን ያህል ሰብአዊ መብት ደፍጠጮች በICC ክስ ተመሰረተባቸው እንዲባል ይፈለጋል? የይስሙላ የመንደር እና የቀበሌ ኮታዎን እንደለመደው እዚሁ በመንደር እና በቀበሌዎ ያድርገው፡፡ እውነተኛውን ዓለም አቀፋዊ የፍትህ አካሉን ስም ማብጠልጠሉን እና ጥለሸት መቀባቱን ግን ፋይዳ አላስገኘለትምና፡፡
ቀደም ሲል እንደነበረው ቅኝ ገዥዎች ሁሉ የነጮቹ የICC ዳኞች እና ዓቃብያነ ሕጎች በፍርድ ቤት እያስቀረቡ የአፍሪካን መሪዎች ይገድላሉ፡፡ በእርግጥ ይህን አባባል ማራመድ የለየለት ድድብና ነው! ICC በአፍሪካ ላይ ሰብአዊ መብቶችን የደፈጠጡትን ወንጀለኞች ለሕግ በማቅረብ ፍትህን ይሰጣል፡፡ ከዚህ አንጻር ዊሊያም ሱቶን ለተባለ አንድ የአሜሪካ የታወቀ ባንክ ዘራፊ ለቀረበለት ጥያቄ የሰጠው እንዲህ የሚለው መልስ ትዝ አለኝ፣ “አንተ ባንኮችን ሁልጊዜ የምትዘርፈው ለምንድን ነው?“ ተብሎ ሲጠየቅ እንዲህ የሚል ቆምጫጫ መልስ ሰጠ፣ “ምክንያቱም ገንዘቡ የሚገኘው እዚያ መሆኑን ስለማውቅ ነው፡፡“ እንደዚሁም ሁሉ ICC የፍርድ ሂደቱን ቀጥሎ ያለው በአፍሪካ ተጠርጣሪዎች ላይ ነው ምክንያቱም አብዛኞቹ ተጥርጣሪ ወንጀለኞች የሚገኙት በአፍሪካ በመሆኑ ነው፡፡ በእርግጥ የሮም ስምምነት መሰረት ያደረገው እ.ኤ.አ ከ2002 ወዲህ ለተፈጸሙት የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ወንጀሎች ብቻ ነው፡፡
አድኃኖም ስለICC ያላው የሕግ ሂደት ግንዛቤ ከእርሱ የፍትህ ስርዓት ጋር በጣም የሚመሳሰል መስሎ ታይቶታል፡፡ እንደ ወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የዝንጀሮ ፍርድ ቤት ሁሉ ለአባላት፣ ለተባባሪዎች እና ለደጋፊዎች አንድ ዓይነት ሕግ ለሌሎች ኢትዮጵያውያን/ት ደግሞ ሌላ ሕግ እንደሚያወጡ ሁሉ አድኃኖም ለICCም በተመሳሳይ መልኩ እንደዚህ ያለ ሕግ መውጣት እንዳለበት ያምናል፡፡ ICC በሰብአዊ መብት ወንጀል ድፍጠጣ ለሚጠየቁ ተጥርጣሪዎች ሁለት ዓይነት ሕግ አያወጣም፡፡ ለሀገር መሪ ወንጀለኞች ለሌሎች የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች ተብሎ የሚወጣ ሕግ የለም፡፡ በአድኃኖም የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ውስጥ ዋናዎቹ የፓርቲው አባሎች ክስ ሊመሰረትባቸው የሚችሉት ከፓርቲያቸው ውጭ ለየት ያለ ሀሳብ ማሰብ ሲጀምሩ ነው፡፡ በዚህን ጊዜ በሙስና ስም ክስ ይመሰረትባቸዋል፡፡ አንግዲህ ወያኔ በእንደዚህ ያለ የሕግ ሂደት ነው ገና ከጫካ ጀምሮ እስከ ወታደራዊው ደርግ ድረስ ሲካሄድ በነበረው የትጥቅ ትግል ዋና ዋና የሚባሉትን ወታደራዊ አዛዦቻቸውን በመግደል ስልጣናቸውን እያመቻቹ እዚህ የደረሱት፡፡
2አድኃኖም ለአፍሪካ ህብረት ያቀረቡት የክርክር ጭብጥ የኡሁሩ እና ሩቶ ህገመንግስታዊ ግዴታዎቻቸውን እና ኃላፊነቶቻቸውን እየተወጡ ነው ወደICC የፍርድ ሂደት ችሎት መቅረብ ያለባቸው፣
አድኃኖም ኬንያታ እና ሩቶ በሰው ልጆች ላይ ስለፈጸሙት በጣም ከፍተኛ የዕልቂት ወንጀል፡ ግድያ፣ አስገድዶ መድፈር፣ የዘር ማጥፋት፣ እና የጦር ወንጀለኝነት ጉዳይ ከምንም አልቆጠረዉም፡፡ ይህ ድርጊት የሚያሳየው ገዳዮች፣ የዘር ማጥፋት ወንጀለኞች፣ እና ሌሎችም አሰቃቂ የሆኑ የሰው ልጅ መብቶችን የሚደፈጥጡ ወንጀለኞች እንደ ወንጀላቸው ሕጉ በሚፈቅደው ሳይሆን እነርሱን እንደተመቻቸው ወደ ICC ብቅ እያሉ የፍርድ ሂደታቸውን ጉዳይ ይከታተሉ ማለት አድኃኖም በሕጉ ላይ ምንም ዓይነት እውቀት እንደሌላቸው ከማሳየቱም በላይ ለሰው ልጅ ህይወት ምን ያህል የቀለለ አመለካከት እንዳላቸው በተጨባጭ ያመላክታል፡፡ ያ ቢደረግ ኖሮ ICC ማን ተብሎ ሊጠራ ነበር? ዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት/International Crimininals Court መባሉ ቀርቶ ዓለም አቀፉ የዝንጀሮዎች ፍርድ ቤት/International Kangaroo Court ነው ሊባል የሚችለው፡፡ ሆኖም ግን በዚህ ጉዳይ ላይ ያለኝን አቋም ለመቀየር እምነት አድሮብኛል፡፡ ይህም የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ምንም ዓይነት የፍትህ አካል ሳይጎበኛቸው በ10ሺዎች እና ከዚያ በላይ የሚቆጠሩ በየእስር ቤቱ ያጎራቸውን ተጠርጣሪ ወገኖቻችንን የፍርድ ሂደት ተጠርጣሪዎቹ በሚመቻቸው መንገድ እያመቻቸ እየተዝናኑ የፍርድ ሂደታቸውን እንዲከታተሉ የሚያደርግ ከሆነ የማቀርበውን ተቃውሞ በሙሉ ውድቅ በማድረግ በነጻ እሰናበታለሁ፡፡
3አድኃኖም ICC ይህንን ቀላል የሆኑ የተጠርጣሪ/ሰለባ አቀራረብን በማራመድ በኬንያ እና በአህጉራችን ብጥብጥ ሊያስነሳ የሚችለውን ነገር ህብረቱውድቅ ሊያደርገው ይገባል የሚል ተማጽዕኖ ለጉባኤው አባላት ማቅረባቸው፣ 
በእርግጥ ይኸ አባባል ፍየሌን ያስገኝልኛል፡! አድኃኖም በኬንያታ እና በሩቶ የተፈጸሙት ወንጀሎች ቀላሎች እና ብዙም እርባና የሌላቸው አድርገው ለማቅረብ ሞክረዋል፡፡ እነዚያ ተጠርጣሪዎች በአንቀጽ 25 (3) (a) ስር በዝርዝር በቀረቡት በሮም ስምምነት በሰው ልጆች ላይ በተፈጸሙ በአምስት ዓይነት ወንጀሎች ነው ክስ የተመሰረተባቸው፡፡ ዝርዝር የህግ ጨብጦችም ሀ) ግድያ መፈጸም፡ በአንቀጽ 7 (1) (a) ስር የተጠቀሰው፣ ለ) ማጋዝ ወይም ደግሞ በግዳጅ ማፈናቀል፡ በአንቀጽ 7 (1) (d) ስር የተጠቀሰው፣ ሐ) አስገድዶ መድፈር፡ በአንቀጽ 7 (1) (g) ስር የተጠቀሰው፣ መ) ማሰቃየት፡ በአንቀጽ 7 (1) (h) ስር የተጠቀሰው፣ ሠ) ሌሎች ሰብአዊ ወንጀሎች፡ በአንቀጽ 7 (1) (k) ስር ተጠቅሶ የተጠቃለሉት ናቸው፡፡
ውንጀላዎቹ 155 ገጽ በያዘ ሰነድ በማስረጃ ተሟልተው እና በመቶዎች የሚቆጠሩ ምስክሮችን ቃል አካትተው በመያዝ የቀረቡ ሲሆን ለህሊና የሚሰቀጥጡ እና ዝርዝር ነበሩ፡፡ በ59 ቀናት ውስጥ ወደ 1,400 የሚሆኑ ሰዎች እንዲያልቁ የተደረጉ ሲሆን ሌሎች 600,000 የሚሆኑት ደግሞ ኬንያ አደገኛ በሆነ መልኩ ወደ የእርስ በእርስ ጦርነት ወደሚመስል ደረጃ በተንሸራተተች ጊዜ ከቤት ንብረታቸው እንዲፈናቀሉ ተደርገዋል፡፡ እ.ኤ.አ በ2007 በኬንያ የተካሄደውን ምርጫ ተከትሎ ተከስቶ በነበረው ውዝግብ በህዝቦች ላይ የደረሰው እልቂት እና ውድመት አድኃኖም እንዳቀረቡት ቀላል የሚባል ነገር አልነበረም፡፡
ምናልባትም እንደዚህ ያሉት ዕልቂቶች እና ስቃዮች ለአድኃኖም ምንም ማለት ላይሆኑ ይችላሉ፡፡ ምናልባትም ለአድኃኖም እንደ እስታሊን ሁሉ የአንድ ሰው ሞት አሰቃቂ ነው፣ የ30 ሚሊዮን ህዝቦች ዕልቂት ግን የቁጥር ጉዳይ ነው፡፡ አሁን በህይወት የሌለው የእርሱ አለቃ እ.ኤ.አ በ2005 በኢትዮጵያ የተካሄደውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ ተከስቶ በነበረው ውዝግብ በእራሳቸው ስልጣን የጦር እና የደህንነት ኃይሉን በቁጥጥራቸው ስር በማድረግ ትዕዛዝ በመስጠት በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰላማዊ ዜጎች እንዲገደሉ አድርጎ ነበር፡፡ ምንም ዓይነት የሕግ ተጠያቂነት አልደረሰቤትም ነበር፡፡ ተጨባጭ የሆኑ መረጃዎችን በመያዝ ኬንያታ እና ሩቶም የመለስን የህዝብ እልቂት በማየት እና ቢያንስ 182 ነፍሰ ገዳዮች እና ሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ የግድያ ሙከራ አድራጊዎች በሕግ ሳይጠየቁ ምንም እንዳልሆኑ ግንዛቤ በመውሰድ ይህንን የፈሪዎች እና የደናቁርት ዕኩይ ድርጊት ከእነርሱ በመኮረጅ እነኬንያታ እና ሩቶ በኬንያ ህዝብ ላይ ፈጽመውታል የሚል የእራሴ እምነት አለኝ፡፡
4ኛ) በሀገር መሪዎች ላይ ምርመራ ማካሄድ እና በሕግ እንዲዳኙ ማድረግ ለኬንያ እና ለአፍሪካ በአጠቃላይ ውስብስብ የሆነ ችግርን ያስከትላል በማለት በአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ላይ ክርክር ማቅረባቸው፣
አድኃኖም ይህንን የመሰል የክርክር ጭብጥ ማቅረቡ ፍጹም በሆነ መልኩ ትክክል ናቸው፡፡ ሟቹ መለስ እ.ኤ.አ በ2005 የተደረገውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ በተከሰተው ውዝግብ በርካታ ንጹሀን ዜጎች እንዲገደሉ ትዕዛዝ በመስጠቱ  ምክንያት በICC ክስ ቢመሰረትበት እና ለሕግ ቢቀርቡ ኖሮ በእርግጠኝነት መናገር እችላለሁ እ.ኤ.አ በ2007 በኬንያ የተደረግውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ተከትሎ በተከሰተው ውዝግብ ሰበብ የኬንያ ህዘቦች እልቂት አይፈጸምም ነበር፡፡
ሆኖም ግን አድኃኖም የሮም ስምምነትን አጠቃላይ ሀሳብ ዘለውታል፡፡ ICC የተቋቋመው እያንዳንዱ ነፍሰ ገዳይ ዘራፊ ከቢሮው በምቹ ተሸከርካሪ ወንበር ተቀምጦ ነገ ደግሞ እነማንን ልግደል፣ ልድፈር፣ ላፈናቅል እያለ በሰው ልጆች ስቃይ ላይ ዳግም ስቃይ እየደገሰ ተዝናንቶ በተቀመጠበት ሁኔታ አይደለም የሕግ ጉዳዩ የሚታየው፡፡ ድርጅቱ ዓላማ አድርጎ የያዘው እጅግ በጣም ጨካኝ የሆኑ የወንጀል ተጠርጣሪዎችን ለፍትህ በማቅረብ ለወንጀል ሰለባዎቹ ፍትህን ለመስጠት እና እንደዚሁም ሁሉ በእብሪት በመነሳሳት ወደፊትም በሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ላይ ተመሳሳይ የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ወንጀሎች እንዳይፈጸሙ ለመማሪያ እንዲሆኑ ማስቻል ጭምር ነው፡፡ ዓለም አቀፍ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት በአፍሪካ ውስጥ ያለምንም ተጠያቂነት በሰው ልጆች ላይ ወንጀል በሚፈጽሙ አምባገነኖች፣ የጦር ወንጀለኞች እና የዘር ማጥፋት ወንጀልን በሚፈጽሙ ተጠርጣሪ  ወንጀለኞች ላይ ICC ፍትህን የሚያጎናጽፍ እርምጃ የሚወስድ በመሆኑ በአፍሪካ መሪዎች፣ አምባገነኖች እና ጦረኞች ላይ አስፈሪ እና አስደንጋጭ ሁኔታ መፍጠሩ ከጥያቄ ሊገባ የሚችል ጉዳይ አይደለም፡፡ በሰው ልጆች ላይ ሰብአዊ ወንጀልን በሚፈጽሙ የአፍሪካ አምባገነኖች ላይ ICC ተገቢ የሆነውን እርምጃ የሚወስድ ከሆነ ይህንን እንደ ትምህርት በመውሰድ በአሁኑ ጊዜ በስልጣን ላይ ያሉት አምባገነኖች ከህግ አግባብ ውጭ የእራሳቸውን ዜጎች መብት ከመደፍጠጥ እንደዚሁም ሁሉ በጫካ ውስጥ ተደብቀው ያሉ ጦረኞች ከተደበቁበት ጫካ ውስጥ በመውጣት በዜጎች ላይ አሰቃቂ እና ጭካኔን የተሞለባት ዕልቂት ከመፈጸም ይታቀባሉ፡፡
አድኃኖም የሀገር መሪዎች በህግ መጠየቅ የለባቸውም ምክንያቱም እነርሱ የሕግ ተጠያቂ የሚሀኑ ከሆነ የአፍሪካ ሉዓላዊነት ይጣሳል ይላሉ፡፡ እንደ ወንጀለኛ አቀራረብ ስነስርዓት ኡሁሩ እና ሩቶ በፈቃደኝነት ለICC ቀረቡ፡፡ ስለዚህ ምንም ዓይነት የሉዓላዊነት ጥያቄ የለም፡፡ አድኃኖም ምን ለማለት ፈልጎ ነው!? እንደ እርሱ አባባል ሉዓላዊነት ማለት ሀገሪቱ፣ ድንበሯ እና ጠቅላላ ህዝቧ መሆናቸው ቀርቶ ሉዓላዊነት ማለት አንዱ ፈላጭ ቆራጭ የሀገር መሪ ተብዬው ነው፣ ስለዚህ እርሱ የሰብአዊ መብት ደፍጥጦ ለICC የፍትህ አካል የሚቀርብ ከሆነ ሉዓላዊነት ተደፈረ ነው ነው እያሉን ያሉት! ለማሰብ ቀርቶ ለመስማትም ያሳፍራል!
የአፍሪካ መሪዎች በሰው ልጆች ላይ ሰብአዊ ወንጀልን ሲፈጽሙ፣ የጦር ወንጀል ሲፈጽሙ እና የዘር ማጥፋት ወንጀልን ሲፈጽሙ ምርመራ እና ለፍትሀ አካል ቀርበው እንዲዳኙ የማይደረገው ለምንድን ነው? አድኃኖም ለዚህ ጥያቄ ምንም ዓይነት መልስ የለዉም፣ ዝም ብሎ ምንም ዓይነት አመክንዮ ሳይኖር በደፈናው ያለምንም ማስረጃ በቀኖናዊነት የሚቀመጥ ካልሆነ በስተቀር ይህ ነው የሚሉት ምሁራዊ አንደበት የላቸውም፡፡ አድሃኃኖም ስለዚህ መሪዎቹ ያለመከሰሳቸው ትክክል ነው ብቻ ነው የሚለው ከዚህ ያለፈ የሚለው ነገር የለም፡፡
አድኃኖም ሆን ብሎ በድንቁርና በሰው ልጆች ላይ የተሻሉ እና መጥፎ የሰብአዊ መብት ወንጀሎችን፣ የጦር ወንጀለኞች እና የዘር ማጥፋት ወንጀለኞችን  የሚፈጽሙ የሚባል ነገር የለም፡፡ እንደዚህ ያሉትን ሰብአዊ ወንጀሎች በሚፈጽሙ በአንድ የሀገር መሪ እና በአንድ የጦር ወንጀለኛ መካከል ምንም ዓይነት የሞራል እና የሕግ ልዩነት የለም፡፡ እንደ አድኃኖም ባለ የተንሻፈፈ እና አመክንዮየለሽ ሀሳብ ከሆነ ከአፍሪካ በቋፍ ላይ ካለ የፖለቲካ ሁኔታ አንጻር ምንም ዓይነት የሰብአዊ መብት ወንጀል የሚፈጽም የሀገር መሪ ፍጹም ሊከሰስ አይችልም፡፡ ከፍተኛ የሆነ እልቂት እና ውድመት ፈጽመው ስልጣንን በኃይል የሚቆጣጠሩ አማጺ መሪዎች እና የጦር አበጋዞች ወይም ደግሞ ምርጫን አጭበርብረው ከህዝብ ፈቃድ ውጭ በስልጣን ማማ ላይ ፊጥ የሚሉ ወንጀለኞች እንደ አድኃኖም ባለ ለእራስ አገልግሎት የቆመ እና አስደንጋጭ መርህ የሚከተል እቡይ ካልሆነ በስተቀር እንደ ማንኛውም ሰብአዊ ፍጡር ለህግ ይቀርባሉ፡፡
እነዚህ የአፍሪካ አምባገነኖች “ርዕሰ ብሄር እና የሀገር መሪ በቢሮ ውስጥ እስካሉ ድረስ በሕግ አይጠየቁም” ይላሉ፡፡ በእርግጥ በስልጣን ላይ የሰብአዊ መብት ደፍጣጮች እንደ ሱዳኑ ኦማር አልባሽር ያሉት ስልጣናቸውን በመጠቀም ለበርካታ አስርት ዓመታት የሰብአዊ መብት እልቂትን እየፈጸሙ የሀገር መሪ በመሆናቸው ምክንያት በሕግ አግባብ የማይሞከሩ አይነኬ፣ ከማንኛውም ዓይነት ተጠያቂነት እና ከሕግ በላይ ናቸው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የአማጺ፣  ወታደራዊ እና የጦር አበጋዝ መሪዎች እነርሱ እራሳቸውን ብቻ ለዚያች ሀገር መድህን እና ጥሩ መሪዎች አድርገው በማቅረባቸው ምክንያት ያለመከሰስ እና ከሕግ ፊት ያለመቅረብ መብት እንዳላቸው ከመጠየቅ ማን ያግዳቸዋል? 
በሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያውን/ ሠራተኞች ስቃይ፣
እ.ኤ.አ ሕዳር 2013 በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች በሳውዲ አረቢያ ጭካኔ በተመላበት ሁኔታ ሲደበደቡ፣ ሲሰቃዩ፣ እና በሳውዲ አረቢያ አገዛዝ፣ በፖሊስ እና በተራው ህዝብ የውርደት ድርጊት ሲፈጸምባቸው ነበር፡፡ በዚያን ወቅት አድኃኖም በታዛዥነት እና እራስን ባዋረደ መልኩ በኢትዮጵያውያን ላይ የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ያካሄደውን አገዛዝ ተጻራሪ በሆነ መልኩ ይቅርታ ጠየቁ፡፡
ይኸ ድርጊት ሌላ ሳይሆን በሽታ ነበር፡፡ በወገኖቻችን ላይ ሲደረግ የነበረው የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ወንጀል ከፍተኛ ደረጃ ላይ በደረሰበት ጊዜ አድኃኖም እንዲህ ብለው ነበር፣ “የሳውዲ ባለስልጣኖች ህገ ወጥ የሆኑ ስደተኞችን መልሶ ወደ ሀገራቸው ለማጋዝ ያወጣውን ፖሊሲ እና ስላስተላለፉት ውሳኔ ኢትዮጵያ ያላትን ክብር ትገልጻለች፡፡“ ይኸ ንግግር በዲፕሎማሲ ቋንቋ አሳዛኝ የሆነ ደንታቢስነት፣ ብቃየለሽነት እና ለተያዘው ቦታ ሊመጥን የማይችል እርባናየለሽነት ነው፡፡ አድኃኖም ኢትዮጵያውያን/ት በሳውዲ አረቢያ በደረሰባቸው ህገወጥ አያያዝ ስሜታቸው የተጎዳ መሆኑን አምነው በመግለጽ ለሳውዲ አረቢያው አምባሳደር ይኸ ተቀባይነት የሌለው ነው በማለት ተናግረው ነበር፡፡ እርሳቸው እና መንግስታቸው ነገሮችን እንዴት ተቆጣጥረው እንዳለ ለማሳየት በሚመስል መልኩ አድኃኖም እንዲህ ብለው ነበር፣ “ወገኖቻችንን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ እና ለመቀበል ዝግጅታችንን ሁሉ ያጠናቀቅን መሆናችንን ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ“
አንድ የእራሱን ዜጎች ሰብአዊ መብት በመርገጥ የሚያዋርድን ሌላ ሀገር ፖሊሲ እንዴት ነው ሊያከብር የሚችለው? አንድ ጤናማ አዕምሮ ያለው ሰው  ዜጎቹ ለተደፈሩበት፣ ለተገደሉበት፣ አካለ ጎደሎ ለሆኑበት፣ለተሰቃዩበት እና በውጭ ሀገር እህት እና ወንድሞቻቸው ለተገደሉባቸው ዜጎቹ እንዴት “ተቀባይነት የለውም” የሚለውን ትርጉመቢስ እና እርባናየለሽ ቃል ምርጫው ያደርጋል? በሳውዲ አረቢያ ሲያልቁ የነበሩትን ወገኖቻችንን ህይወት ለመታደግ እና ግድያውን ለማስቆም አድኃኖም ለሳውዲ አረቢያ አምባሳደር መጮህ ነበረባቸው፡፡ እንዴት አንድ ወገኖቹ የግድያ ሰለባ ሲሆኑ እና ሰብአዊ መብታቸው ተደፍጥጦ እየተሰቃዩ ባሉበት ሁኔታ ግላዊ ጭንቀት እና ሀዘን ይሰማኛል ሊል ይችላል? አንድ ሰው እንዴት የዜጎቹ መሰረታዊ የሰብአዊ መብቶች በአምባገነኖች ሲጣሱ እና ሲደፈጠጡ እንዴት ምንም ነገር ባለማድረግ ቀዝቅዞ እና የሰብአዊነት ርህራሄ ሳይኖረው ዝም ብሎ ይመለከታል?  እንዴት አንድ ሰው ዜጎቹ ስቃያቸውን እየተቀበሉ እያየ በመበሳጨት ዲፕሎማሲያዊ ቁጣውን እና ንዴቱን መግለጽ ይሳነዋል? በሺዎች ለሚቆጠሩ ስለእህቶቻችን እና ወንድሞቻችን በሞት እና በሽረት መካከል መኖር እየተነጋገርን ነው፡፡ ደህና ይኸ ነው እንግዲህ አሁን በቅርቡ ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁ ባለስልጣን እየሰራው ያለው ስራ!
እ.ኤ.አ ጥቅምት 2014 የአድኃኖም አንዱ ደጋፊ በሆነው ዘራፊ የዲፕሎማት ከለላ አለው ተብሎ በዋሽንግተን ዲ.ሲ በኢትዮጵያ ኤምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ጥይት ስለተኮሰው እና ያልተጠበቀ የዲፕሎማሲያዊ ቀውስ እንዲከተል ስላደረገው ሁከት ፈጣሪ ስለነበረው እብሪተኛ መናገር እችላለሁ፡፡ በዋሽንግተን ዲ.ሲ የዲፕሎማቶች መዝገብ ላይ ተቀርጾ የሚገኘው ሰነድ እንደሚያሳየው የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብሰብ ሌባ ዲፕሎማት ተብዬ ሰላማዊ አመጸኞችን ከኤምባሲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ለማባረር በኤምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ጥይት በመተኮስ ከዓለም የመጀመሪያ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡
አድኃኖም በዓለም ዋናዋ እና የመጀመሪያዋ የዲፕሎማት ማዕከል በሆነችው በዋሽንግተን ዲ.ሲ ያንን የመሰለ ወሮበላ ምንም ዓይነት የዲፕሎማሲ ልምድ፣ ስልጠና ወይም ደግሞ እንደ ከደህንነት አታሸ ሙያ ጋር ምንም ዓይነት ክህሎት የሌለውን ተራ ማይም ልከው ነበር፡፡ ደህና እስከ አሁን ድረስ ስለወሮበላ ዲፕሎማሲ እና ስለዘራፊ ዲፕሎማት ብዙ ብለናል፡፡
በእውነት የብሩክሊንን ድልድይ እጅግ በጣም ርካሽ በሆነ ዋጋ ለሽያጭ ለማቅረብ ዕድሉን አግኝቻለሁ፡፡ የማዲሰን እስኩዌር ጋርደን ህንፃን እንደ ጉርሻ በተጨማሪነት አባሪ በማድረግ እሰጣለሁ፡፡
አድኃኖም ፍላጎት ሊኖረህ ይችላል ?
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!